“ሥራህ ለራስህ አለቃ ነው” – ወ/ሮ መስታወት መስቀሌ በአስፋው አማረ አንድ ሰው ህይወቱን ለማሻሻል...
ንጋት ጋዜጣ
“በእኔ ተስፋ የነበራት እናቴ ብቻ ነበረች” – ወጣት ሹኩሪ ኢብራሂም በጋዜጣው ሪፖርተር በሥራ አጥነት እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚፈተኑ አካል ጉዳተኞች በርካቶች ናቸው። ይሁንና አካል ጉዳተኝነታቸው ከህልማቸው ሳይገድባቸው አስቸጋሪ ፈተናዎቻቸውን ተጋፍጠው ለስኬት የበቁም ቁጥራቸው በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ ከእነዚህ መካከል የዛሬው የችያለሁ አምድ ባለታሪካችን ይጠቀሳል፡፡ ትልቅ ቦታ የመድረስ ህልም ስለነበረው በልጅነቱ ረዥም መንገድ በዱላ ድጋፍ እየተጓዘ ነበር የሚማረው፡፡ ይህም ከበርካታ ተግዳሮቶቹ መካከል አንዱ ነው። ስሙ ሽኩሪ ኢብራሂም ይባላል። ትውልድ እና ዕድገቱ ሀላባ ዞን ምዕራብ ጎርጣንቾ ቀበሌ÷ ልዩ ስሙ ወርቾ በሚባል የገጠር መንደር ነው፡፡ በልጅነቱ እንደ እኩዮቹ ከሰፈር ልጆች ጋር እየቦረቀ ይጫወት ነበር። ይሁን እንጂ ባልታወቀ ምክንያት እግሩ ላይ ጉዳት ደረሰበት፡፡ ድንገት ወድቆ እናቱ ሊያነሱት ሲሉ ግራ እግሩ አልዘረጋ እንዳላቸው ሲናገሩ ሰምቷል፡፡ ዘግይተው ወደ ህክምና ወስደውት ስለነበር ምክንያቱን መለየት አልቻሉም፡፡ ዶክተሮቹ በጊዜ ህክምና ቢያገኝ ተስፋ ይኖረው ነበር፥ በማለት እናቱ የነገሩትን ያስታውሳል፡፡ ዕድሜው ለትምህርት ሲደርስ በ1997 ዓ.ም ትምህርት ቤት የገባ ሲሆን፥ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ሀላባ ዞን፥ አልቆጫ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል፡፡ በነበረበት አካባቢ ከ8ኛ ክፍል በላይ ትምህርት ቤት ስላልነበረ ከገጠር ወደ ከተማ እየተመላለሰ ነበር የሚማረው፡፡ በዚህ የተነሳ ብዙ እንግልቶችን አሳልፏል፡፡ መመላለሱ ሲከብደው ችግሩን እንዲቀርፉለት የሚመለከታቸውን አካላት ድጋፍ ቢጠይቅም ምላሽ አላገኝም፡፡ ይሁን እንጂ፥ በጎ ሰዎች አይጠፉምና ከቀበሌው ሊቀመንበር አቶ አህመድ አደም ጋር የሚገናኝበት አጋጣሚ ተፈጠረ። እየተመላለሰ መማሩን ሰምተው ከተማ ላይ ቤት ስለነበራቸው አንድ ክፍል ቤት እንደሰጡት ገልፆ 9ኛ ክፍልን ያለ እንግልት መማሩን አጫውቶናል፡፡ ሽኩሪ ገና በልጅነቱ ነበር ኑሮን ለማሸነፍ ይተጋ የነበረው፡፡ ገጠር እያለ የሰፈር ልጆችን ፀጉራቸውን አስተካክሎ ገቢ ያገኝ ነበር፡፡ ያ ልምድ ዳብሮ ከተማ ሲገባም ፀጉር ቤቶች ላይ በትርፍ ሰዓቱ እየሰራ መጠነኛ ክፍያ ማግኘት ጀመረ። በሚያገኘው ገንዘብ የቤት ኪራይ እየከፈለ 10ኛ ክፍልን ሀላባ መሰናዶ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል፡፡ ...
በካሡ ብርሃኑ “ዝቅ ብሎ የሠራ ቀና ብሎ ይሄዳል” የሚል ፅኑ አቋም አላቸው፡፡ ለዚህም ይመስላል...
በኢያሱ ታዴዎስ ከ2 ሺህ ዓመታት በላይ ታሪክ እንዳለው የሚነገርለት ተወዳጁ የዓለማችን ቁጥር 1 ስፖርት...
በደረጀ ጥላሁን የሳምንቱ የንጋት እንግዳችን አቶ ታረቀኝ መናሞ ይባላሉ፡፡ ትውልድና እድገታቸው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል...
ከመሀረብ መንካት እስከ ኦሎምፒክ ሪባን ማቋረጥ በአንዱዓለም ሰለሞን አገሬን አየሁዋት ሰው ሀገር ሰማይ ላይከኦሎምፒክ...
“ትዕግስት ለሾፌሮች ትልቅ መሳሪያ ነው” ሾፌር ሞገስ ለገሠ በጋዜጣው ሪፖርተር በአሽከርካሪነት ሙያ ለረጅም ዓመታት...
ሽምግልና እና ሰርግ ሲምታታ በኢያሱ ታዴዎስ በሀገራችን ሚያዚያ ከጥር በመቀጠል የሰርግ ወር ተደርጎ ይወሰዳል።...
በአለምሸት ግርማ ንቁ ማህበረሰብን በማፍራት ሂደት ውስጥ የወላጆች ሚና ትልቁን ድርሻ ይይዛል። ልጆች በልጅነታቸው...
የአሥም በሽታ ቅድመ መከላከል ላይ ትኩረት መደረግ እንዳለበት ተገለፀ በቤተልሄም አበበ ለአስም በሽታ ተጋላጭነት...