አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
“ጽዱ ኢትዮጵያን ባህል እናድርግ” በሚል መሪ ቃል ሁለተኛው ዙር የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቦንጋ ከተማ አካሂዷል።
በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የተጀመሩ የጽዱ ኢትዮጵያ ዘመቻዎች በሁሉም አካባቢዎች ተጠናከረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
አካባቢን ማጽዳትና መንከባከብ የሁሉም ተግባር ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል።
የኢፌዴሪ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሚ እንደ ሀገር በተጀመረው የንቅናቄ ስራ ከ15 ሚሊየን በላይ የህብረተረብ ክፍሎች በቀጥታ የሚሳተፉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመጀመሪያ ዙሪ “ብክለት ይብቃ ውበት ይንቃ” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የንቅናቄ መድረክ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን የክልሉ ደን አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኢንጂነር አስራት ገብሬማርያም በሪፖርት አቅርበዋል።
“ጽዱ ኢትዮጵያን ባህል እናድርግ” በሚሪ ቃል የተጀመረው የንቅናቄ መድረክ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ይቀጥላል ብለዋል።
በከተሞች የቆሻሻ አወጋገድ ላይ የወጣ ክልላዊ አዋጅ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በክረምት በጎ ፊቃድ አገልግሎት ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትና የቀጣይ ስራ እቅድ በክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ በወ/ሮ ገነት መኩሪያ ቀርቧል።
በመድረኩ የተገኙ አካላት በበኩላቸው የተጀመሩ ስራዎችን በማስቀጠል የተያዘው እቅድ እንዲሳካ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል።
በንቅናቄ መድረኩ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ : አካሉ ወልደኢየሱስ- ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ