ጥራት ያለው ኮረሪማ ለገበያ ለማቅረብና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ትኩረት መደረጉን የአሪ ዞን ቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በበጀት አመቱ ዞኑ ከ15 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኮረሪማ መሸፈኑንም ገልጿል።
በዞኑ በኮረሪማ ምርት የተሰማሩ የሰሜን አሪ እና ዎባ አሪ ወረዳ አርሶአደሮች ከዘርፉ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የምርቱን ጥራት የሚቀንሱ ተግባራትን ለመግታት በጋራ መሥራት እንደሚያስፈልግ በኮረሪማ ንግድ የተሰማሩ ነጋዴዎች ገልጸዋል።
ጥራት ያለው ኮረሪማን ለዓለም ገበያ ለማቅረብና የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለመጨመር ትኩረት መደረጉን በዞኑ የሰሜን ኣሪ እና የዎባ አሪ ወረዳ አስተዳዳሪዎች ገልፀዋል።
የኣሪ ዞን የቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ርብቃ እሳቱ፤ ጥራት ያለውን ኮረሪማ ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መደረጉን ገልፀው፤ በዞኑ 15 ሺህ ሄክታር መሬት በኮረሪማ መሸፈኑን አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
የቡና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ገለጹ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸውን ተቋማት የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ ጀመረ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ከ12 ቢሊየን ብር በላይ በጀት 471 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ