ጥራት ያለው ኮረሪማ ለገበያ ለማቅረብና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ትኩረት መደረጉን የአሪ ዞን ቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በበጀት አመቱ ዞኑ ከ15 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኮረሪማ መሸፈኑንም ገልጿል።
በዞኑ በኮረሪማ ምርት የተሰማሩ የሰሜን አሪ እና ዎባ አሪ ወረዳ አርሶአደሮች ከዘርፉ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የምርቱን ጥራት የሚቀንሱ ተግባራትን ለመግታት በጋራ መሥራት እንደሚያስፈልግ በኮረሪማ ንግድ የተሰማሩ ነጋዴዎች ገልጸዋል።
ጥራት ያለው ኮረሪማን ለዓለም ገበያ ለማቅረብና የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለመጨመር ትኩረት መደረጉን በዞኑ የሰሜን ኣሪ እና የዎባ አሪ ወረዳ አስተዳዳሪዎች ገልፀዋል።
የኣሪ ዞን የቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ርብቃ እሳቱ፤ ጥራት ያለውን ኮረሪማ ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መደረጉን ገልፀው፤ በዞኑ 15 ሺህ ሄክታር መሬት በኮረሪማ መሸፈኑን አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በያዝነው ዓመት አስከ ጥቅምት ወር ድረስ 2 መቶ 50 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መላኩን የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የምርምር ተቋማት ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የግብርናውን ስራ ውጤታማ እንዲያደርጉ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ስራ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ኢንስቲትዩት አስታወቀ
የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ እና ያለብክነት ሊሰበሰብ እንደሚገባ የባኮ ዳውላ ኣሪ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አሳሰበ