ጥራት ያለው ኮረሪማ ለገበያ ለማቅረብና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ትኩረት መደረጉን የአሪ ዞን ቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በበጀት አመቱ ዞኑ ከ15 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኮረሪማ መሸፈኑንም ገልጿል።
በዞኑ በኮረሪማ ምርት የተሰማሩ የሰሜን አሪ እና ዎባ አሪ ወረዳ አርሶአደሮች ከዘርፉ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የምርቱን ጥራት የሚቀንሱ ተግባራትን ለመግታት በጋራ መሥራት እንደሚያስፈልግ በኮረሪማ ንግድ የተሰማሩ ነጋዴዎች ገልጸዋል።
ጥራት ያለው ኮረሪማን ለዓለም ገበያ ለማቅረብና የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለመጨመር ትኩረት መደረጉን በዞኑ የሰሜን ኣሪ እና የዎባ አሪ ወረዳ አስተዳዳሪዎች ገልፀዋል።
የኣሪ ዞን የቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ርብቃ እሳቱ፤ ጥራት ያለውን ኮረሪማ ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መደረጉን ገልፀው፤ በዞኑ 15 ሺህ ሄክታር መሬት በኮረሪማ መሸፈኑን አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የከምባታ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ
በጎፋ ዞን በአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ8 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ችግኞች ለመትከል ዝግጅት መጠናቀቁን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ
ነገ በአንድ ቀን ጀምበር 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የደቡብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ