ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ክልል አቀፍ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ የካቲት 30/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት ”በመደመር መንግስት እይታ የኃይማኖት ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ክልል አቀፍ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)፣ የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እና የክልሉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ግለሰቦች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: ኤደን ተረፈ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኮረሪማ ምርት እየለማ መሆኑ ተገለጸ
በጎፋ ዞን ከ12 ሺህ በላይ ተማሪዎች ክልላዊ የ6ኛ ክፍል ፈተና እየተሰጠ ነው
የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በመመለስ በኩል ከመንግስት ጥረት ባለፈ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና የጎላ መሆኑን የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ ተናገሩ