ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ክልል አቀፍ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ የካቲት 30/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት ”በመደመር መንግስት እይታ የኃይማኖት ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ክልል አቀፍ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)፣ የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እና የክልሉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ግለሰቦች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: ኤደን ተረፈ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የእምነት ተቋማት ለአገረ መንግስት ግንባታ ቁልፍ ሚና ያላቸው በመሆኑ ለሀገር ብልጽግና ኃይል አድርጎ መጠቀም እንደሚገባ ተመላከተ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የኢትዮጵያ ብልፅግና እንዲረጋገጥ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከቷ ተገለጸ
የሙስሊሙ ማህበረሰብ በረመዳን ጾም ወቅት የሀይማኖቱ አስተምህሮ የሆነውን በጎ ተግባራት በማከናወን ማሳለፍ እንደሚገባ ተገለጸ