የእምነት ተቋማት ለአገረ መንግስት ግንባታ ቁልፍ ሚና ያላቸው በመሆኑ ለሀገር ብልጽግና ኃይል አድርጎ መጠቀም እንደሚገባ ተመላከተ
ሀዋሳ፡ የካቲት 30/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የመደመር መንግስት ለሀይማኖት ተቋማት እኩልነትና ሰላም ግንባታ” በሚል መሪ ቃል ከኣሪ ዞን ሁሉም ወረዳዎችና የከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የሀይማኖት ተቋማት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።
በመደመር መንግስትና የሀይማኖት ተቋማት መካከል ያሉ ልዩነትቶችና የግንኙነት መርሆዎች ላይ ያተኮረው የምክክር መድረክ በኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ የተለያዩ አዳራሾች እየተካሄደ ነው።
በመድረኮቹ እንደ ሀይማኖት ተቋማቱ ባህሪያት የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተካሄ ነው።
“የመደመር መንግስት ለሀይማኖት ተቋማት እኩልነትና ሰላም ግንባታችን” በሚል መርህ እየተካሄደ በሚገኘው መድረክ ከኣሪ ዞን ወረዳዎችና የከተማ አስተዳደር መዋቅሮች የተውጣጡ የሁሉም የሀይማኖት ተቋቋማት አመራሮችና ተወካዮቻቸው እየተሳተፉበት ይገኛል።
ዘጋቢ: ወንድሜነህ አድማሱ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የኢትዮጵያ ብልፅግና እንዲረጋገጥ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከቷ ተገለጸ
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ክልል አቀፍ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
የሙስሊሙ ማህበረሰብ በረመዳን ጾም ወቅት የሀይማኖቱ አስተምህሮ የሆነውን በጎ ተግባራት በማከናወን ማሳለፍ እንደሚገባ ተገለጸ