የማኅበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ሲሳይ አስማረ እንደገለጹት÷ የዘርፉ ዳግም መነቃቃት ለላኪዎች ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሯል።
የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምረው የሚልኩ ኢንዱስትሪዎች ለውጭ ምንዛሬ ግኝት አስተዋጽኦ እያደረጉ
መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ማኅበሩ 230 ሺህ ሜትሪክ ቶን ሰሊጥ ወደ ውጪ ለመላክ መዘጋጀቱን ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡
ለአርሶ አደሮች ከማሳ ጀምሮ አጠቃላይ የምርት ሂደት ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በዱባይ ዓለም አቀፍ የቅባት እህሎች ኮንፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ሬንዲ ዳኩሬት ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ በሰጠችው ልዩ ትኩረት ጥራት ያላቸው ምርቶች ለዓለም ገበያ እየቀረቡ ነው ብለዋል፡፡

More Stories
ግብር ለአንድ ሀገር ህልውና መረጋገጥ እና ህብረተሰቡ ለሚያነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ወሳኝ በመሆኑ በአሰባሰብ ወቅት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በሀዲያ ዞን የሌሞ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በሩብ ዓመቱ 3.7 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወሰነች ቶማስ ገለጹ
የማር ምርት እጅግ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በጎምቦራ ወረዳ በንብ ማነብ ስራ የተሠማሩ አርሶአደሮች ተናገሩ