የማኅበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ሲሳይ አስማረ እንደገለጹት÷ የዘርፉ ዳግም መነቃቃት ለላኪዎች ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሯል።
የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምረው የሚልኩ ኢንዱስትሪዎች ለውጭ ምንዛሬ ግኝት አስተዋጽኦ እያደረጉ
መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ማኅበሩ 230 ሺህ ሜትሪክ ቶን ሰሊጥ ወደ ውጪ ለመላክ መዘጋጀቱን ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡
ለአርሶ አደሮች ከማሳ ጀምሮ አጠቃላይ የምርት ሂደት ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በዱባይ ዓለም አቀፍ የቅባት እህሎች ኮንፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ሬንዲ ዳኩሬት ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ በሰጠችው ልዩ ትኩረት ጥራት ያላቸው ምርቶች ለዓለም ገበያ እየቀረቡ ነው ብለዋል፡፡
More Stories
የቡና ልማትና ግብይትን አስመልክተው የሚወጡ ዓለም-አቀፍ ህጎችን አክብሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው የጥቁር ህዝቦች ኩራት ነው – የኮሬ ዞን አስተዳደር
ግድባችን የአባይ ዘመን ትውልድ ትክክለኛ ሀሳብ፣ በትክክለኛ ጊዜ የገነባነው ዘመን ተሻጋሪ ቅርሳችን ነው ሲሉ በደቡብ ኦሞ ዞን የበና ፀማይ ወረዳ ነዋሪዎች ገለፁ