የማኅበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ሲሳይ አስማረ እንደገለጹት÷ የዘርፉ ዳግም መነቃቃት ለላኪዎች ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሯል።
የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምረው የሚልኩ ኢንዱስትሪዎች ለውጭ ምንዛሬ ግኝት አስተዋጽኦ እያደረጉ
መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ማኅበሩ 230 ሺህ ሜትሪክ ቶን ሰሊጥ ወደ ውጪ ለመላክ መዘጋጀቱን ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡
ለአርሶ አደሮች ከማሳ ጀምሮ አጠቃላይ የምርት ሂደት ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በዱባይ ዓለም አቀፍ የቅባት እህሎች ኮንፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ሬንዲ ዳኩሬት ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ በሰጠችው ልዩ ትኩረት ጥራት ያላቸው ምርቶች ለዓለም ገበያ እየቀረቡ ነው ብለዋል፡፡

More Stories
በሆሣዕና ከተማ የሚገነቡ ሆቴሎች የከተማውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን በሣላማጎ ወረዳ በሌማት ትሩፋት በቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ