የማኅበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ሲሳይ አስማረ እንደገለጹት÷ የዘርፉ ዳግም መነቃቃት ለላኪዎች ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሯል።
የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምረው የሚልኩ ኢንዱስትሪዎች ለውጭ ምንዛሬ ግኝት አስተዋጽኦ እያደረጉ
መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ማኅበሩ 230 ሺህ ሜትሪክ ቶን ሰሊጥ ወደ ውጪ ለመላክ መዘጋጀቱን ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡
ለአርሶ አደሮች ከማሳ ጀምሮ አጠቃላይ የምርት ሂደት ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በዱባይ ዓለም አቀፍ የቅባት እህሎች ኮንፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ሬንዲ ዳኩሬት ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ በሰጠችው ልዩ ትኩረት ጥራት ያላቸው ምርቶች ለዓለም ገበያ እየቀረቡ ነው ብለዋል፡፡
More Stories
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ በጂንካ ከተማ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ጎዳና የወጡ ህጻናትን ሥራ ዕድል እንዲያገኙ የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ ነው
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በማህበረሰብ ድጋፍ ከ2.6 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በከምባታ ዞን ለሀምቦ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
ከልማት አጋሮች የሚገኘውን የበጀት ድጋፍ ለታለመለት አላማ በማዋል ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ገለጸ