የማኅበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ሲሳይ አስማረ እንደገለጹት÷ የዘርፉ ዳግም መነቃቃት ለላኪዎች ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሯል።
የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምረው የሚልኩ ኢንዱስትሪዎች ለውጭ ምንዛሬ ግኝት አስተዋጽኦ እያደረጉ
መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ማኅበሩ 230 ሺህ ሜትሪክ ቶን ሰሊጥ ወደ ውጪ ለመላክ መዘጋጀቱን ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡
ለአርሶ አደሮች ከማሳ ጀምሮ አጠቃላይ የምርት ሂደት ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በዱባይ ዓለም አቀፍ የቅባት እህሎች ኮንፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ሬንዲ ዳኩሬት ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ በሰጠችው ልዩ ትኩረት ጥራት ያላቸው ምርቶች ለዓለም ገበያ እየቀረቡ ነው ብለዋል፡፡

More Stories
የሚተከሉ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ መርሐ ግብሮች የአየር ሚዛንን ከማስጠበቅ ባሻገር በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተገለጸ
በክልሉ 295 የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመለየት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን ግብርና መምሪያ አስተባባሪነት የ2018 ዓ.ም የመኸር ወቅት የተቀናጀ የግብርና ስራዎች ንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል