የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸውን ተቋማት የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ: ጥር 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸውን ተቋማት የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ማድመጥ ጀምሯል።
የክልሉ ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ግብርና ቢሮ፣ ባህልና ቱሪዝም ፣ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ፣ የደንና አከባቢ ጥበቃ ቢሮ የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ይገመግማል ተብሎ ይጠበቃል።
በክልሉ የአርብቶ አደር አካባቢዎች በ2017 መጀመሪያ ግማሽ አመት የተከናወኑ ጠንካራ የልማት የመልካም አስተዳደር ስኬቶች በሪፖርቱ የተመላከተ ሲሆን፥ የግብርናና ገጠር ልማት ቋሚ ኮሚቴ በቀረበው ሪፖርት ላይ ጥያቄዎችንና ግብረ መልሶችን እየሰጠ ነው።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጠንክር ጠንካ ጨምሮ የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የተቋማቱ የቢሮ ኃላፊዎች እንዲሁም የማኔጅመንት አባላት እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
ወጣቱ ትዉልድ በግብርናዉ ዘርፍ ያሉ አማራጮችን ተጠቅሞ የኢኮኖሚ ባለቤት እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ባሌ ከተማ አስተዳደር ሶዶ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፈቱ
በከተማ ያለውን ህገወጥ የንግድ ስርዓት እና ኮንትሮባንድን በማስቀረት ህጋዊ ነጋዴዎችን የመደገፍ እና የማበረታታት ስራ እንደሚሰራ ተገለጸ