በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የአርባ ምንጭ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ፣ የአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን አርባ ምንጭ ቅርንጫፍ በጋራ በመሆን ከ300 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የዓይነት ድጋፍ አደረጉ
ተቋማቱ በአደጋው ምክንያት ሕይወታቸውን ባጡና ጉዳት በደረሰባቸው ወገኖች የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል።
በጋራ ያሰባሰቡት አልባሳትና የምግብ ግብዓቶች “የወገን ለወገን ደራሽነት” ማሳያ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ አሁን የተደረገው ድጋፍ የመጀመሪያ ዙር መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም ተጎጂዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ውስጥ ተቋማቱ የበኩላቸውን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ድጋፉን የተረከቡት የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ ተስፉጽዮን ዘነበ በበኩላቸው ተቋማቱ ላደረጉት ድጋፍ በዞኑ አስተዳደርና በተጎጂዎች ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ዘጋቢ ፡ ተመኙህ ገረሱ-ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ