የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 09/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 500ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ዋና እምባ ጠባቂ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ እንደ ሀገር የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀው፥ የ500ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ለአደጋው ተጎጂዎች ማድረጉን ተናግረዋል።
ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት ባስተላለፉት መልእክት፥ በቀጣይም ከአደጋው የተረፉ ወገኖች ተገቢው ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ አመላክተዋል።
ተቋሙም በሚደረጉ ድጋፎች የበኩሉን እንደሚወጣ ገልፀዋል።
የጋሞ ሀገር ሽማግሌ ተቋሙ ላደረገው ድጋፍና ላሳየው አለኝታነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘውዱ

More Stories
“ጠንካራ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት የትምህርት ጥራትን ያስጠብቃል“ – ደስታ ገነሜ (ዶ/ር)
የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸዉ ተገለፀ
በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የአርባ ምንጭ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ፣ የአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን አርባ ምንጭ ቅርንጫፍ በጋራ በመሆን ከ300 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የዓይነት ድጋፍ አደረጉ