የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 09/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 500ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ዋና እምባ ጠባቂ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ እንደ ሀገር የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀው፥ የ500ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ለአደጋው ተጎጂዎች ማድረጉን ተናግረዋል።
ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት ባስተላለፉት መልእክት፥ በቀጣይም ከአደጋው የተረፉ ወገኖች ተገቢው ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ አመላክተዋል።
ተቋሙም በሚደረጉ ድጋፎች የበኩሉን እንደሚወጣ ገልፀዋል።
የጋሞ ሀገር ሽማግሌ ተቋሙ ላደረገው ድጋፍና ላሳየው አለኝታነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘውዱ

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ