‎የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ

‎የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ

‎ሀዋሳ፡ መጋቢት 09/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 500ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል።

‎የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ዋና እምባ ጠባቂ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ እንደ ሀገር የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀው፥ የ500ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ለአደጋው ተጎጂዎች ማድረጉን ተናግረዋል።

‎ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት ባስተላለፉት መልእክት፥ በቀጣይም ከአደጋው የተረፉ ወገኖች ተገቢው ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ አመላክተዋል።

‎ተቋሙም በሚደረጉ ድጋፎች የበኩሉን እንደሚወጣ ገልፀዋል።

‎የጋሞ ሀገር ሽማግሌ ተቋሙ ላደረገው ድጋፍና ላሳየው አለኝታነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘውዱ