የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 09/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 500ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ዋና እምባ ጠባቂ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ እንደ ሀገር የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀው፥ የ500ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ለአደጋው ተጎጂዎች ማድረጉን ተናግረዋል።
ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት ባስተላለፉት መልእክት፥ በቀጣይም ከአደጋው የተረፉ ወገኖች ተገቢው ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ አመላክተዋል።
ተቋሙም በሚደረጉ ድጋፎች የበኩሉን እንደሚወጣ ገልፀዋል።
የጋሞ ሀገር ሽማግሌ ተቋሙ ላደረገው ድጋፍና ላሳየው አለኝታነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘውዱ

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ