ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በወልቂጤ ከተማ ከ127 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባውን ሞዴል የማህበረሰብ ትምህርት ቤት የምረቃ ስነ-ስርዓት በመከናወን ላይ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 27/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በጉብሬ ክፍለ ከተማ ከ127 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባውን ሞዴል የማህበረሰብ ትምህርት ቤት (ከ1ኛ-8ኛ) የምረቃ ስነ-ስርዓት በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አስከብር ወልዴ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፋሪስ ደሊል፣ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድርን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ ከፌደራል፣ ከክልል፣ ከዞንና ከከተማ አስተዳደር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ፍስሃ ክፍሌ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የማር ምርት እጅግ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በጎምቦራ ወረዳ በንብ ማነብ ስራ የተሠማሩ አርሶአደሮች ተናገሩ
ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በደረሰ የግብርና ልማት ላይ አደጋ እንዳያስከትል ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ ተገለጸ
የገጠር ኮሪደር ኤኒሼቲቭ የገጠርሪቱን ኢትዮጵያ አኗኗር ዘይቤ በእጅጉ የሚያዘምን መሆኑ ተገለጸ