ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በወልቂጤ ከተማ ከ127 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባውን ሞዴል የማህበረሰብ ትምህርት ቤት የምረቃ ስነ-ስርዓት በመከናወን ላይ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 27/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በጉብሬ ክፍለ ከተማ ከ127 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባውን ሞዴል የማህበረሰብ ትምህርት ቤት (ከ1ኛ-8ኛ) የምረቃ ስነ-ስርዓት በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አስከብር ወልዴ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፋሪስ ደሊል፣ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድርን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ ከፌደራል፣ ከክልል፣ ከዞንና ከከተማ አስተዳደር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ፍስሃ ክፍሌ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በያዝነው ዓመት አስከ ጥቅምት ወር ድረስ 2 መቶ 50 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መላኩን የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የምርምር ተቋማት ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የግብርናውን ስራ ውጤታማ እንዲያደርጉ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ስራ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ኢንስቲትዩት አስታወቀ
የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ እና ያለብክነት ሊሰበሰብ እንደሚገባ የባኮ ዳውላ ኣሪ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አሳሰበ