ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በወልቂጤ ከተማ ከ127 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባውን ሞዴል የማህበረሰብ ትምህርት ቤት የምረቃ ስነ-ስርዓት በመከናወን ላይ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 27/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በጉብሬ ክፍለ ከተማ ከ127 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባውን ሞዴል የማህበረሰብ ትምህርት ቤት (ከ1ኛ-8ኛ) የምረቃ ስነ-ስርዓት በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አስከብር ወልዴ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፋሪስ ደሊል፣ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድርን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ ከፌደራል፣ ከክልል፣ ከዞንና ከከተማ አስተዳደር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ፍስሃ ክፍሌ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ
በክልሉ የሚከናውኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሊሆኑ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ገለፁ
የአፈርና ውሃ ጥበቃ በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ