ከ346 ሺህ ኩንታል በላይ ቡናን ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅርብ እየተሰራ እንደሚገኝ የቤንች ሸኮ ዞን ግብርናና አካባቢ ጥበቃ ህብረት ሥራ መምሪያ አስታወቀ
በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ ከ35 ሺህ ሄክታር በላይ የቡና ማሳ ያለ ሲሆን ከ25ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ምርት የሚሰጥ መሆኑን የወረዳው ምክትል አስተዳደሪና የግብርናና አካባቢ ጥበቃ ህብረት ሥራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኪዳነ ሽቅ ተናገረዋል።
ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚላከውን የቡና ምርትን ከማሳደግ አኳያ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ በሄክታር
ከ7 እስከ 9 ኩንታል ምርት እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ኪዳኔ በጀንፈል ሲሆን በሄክታር ከ25 እስከ 30 ኩንታል ይገኛል ብለዋል።
በወረዳው በስፋት ከሚመረተው ከቡና ምርት ጎን ለጎን ቅመማ ቅመም ትኩረት ተሰጥተው የሚሰራ ሲሆን ኮረሪማ፣ ቁንዶ በረበሬ፣ ዕረድ እና ዝንጅብል ተጠቃሾች መሆናቸውን ኃላፊው አብራርተዋል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡናን በብዛትና በጥራት ከሚያመረቱ ዞኖች መካከል የቤንች ሸኮ ዞን አንዷ መሆኗም ተገልጿል።
በበጀት ዓመቱ ከ346 ሺህ ኩንታል በላይ ቡናን ለአለም ገቢያ ለማቅርብ እየተሰራ እንደሚገኝ የዞኑ ግብርናና አካባቢ ጥበቃ ህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ጉብላ ተናገረዋል።
ዘጋቢ፦ አብዲሳ ዮናስ ከሚዛን ጣቢያችን።
More Stories
ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ግብዓቶች አጠቃቀም ማሻሻልና ማዘመን እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
ጥራት ያለው ኮረሪማ ለገበያ ለማቅረብና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ትኩረት መደረጉን የአሪ ዞን ቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የቡና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ገለጹ