ከ346 ሺህ ኩንታል በላይ ቡናን ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅርብ እየተሰራ እንደሚገኝ የቤንች ሸኮ ዞን ግብርናና አካባቢ ጥበቃ ህብረት ሥራ መምሪያ አስታወቀ
በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ ከ35 ሺህ ሄክታር በላይ የቡና ማሳ ያለ ሲሆን ከ25ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ምርት የሚሰጥ መሆኑን የወረዳው ምክትል አስተዳደሪና የግብርናና አካባቢ ጥበቃ ህብረት ሥራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኪዳነ ሽቅ ተናገረዋል።
ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚላከውን የቡና ምርትን ከማሳደግ አኳያ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ በሄክታር
ከ7 እስከ 9 ኩንታል ምርት እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ኪዳኔ በጀንፈል ሲሆን በሄክታር ከ25 እስከ 30 ኩንታል ይገኛል ብለዋል።
በወረዳው በስፋት ከሚመረተው ከቡና ምርት ጎን ለጎን ቅመማ ቅመም ትኩረት ተሰጥተው የሚሰራ ሲሆን ኮረሪማ፣ ቁንዶ በረበሬ፣ ዕረድ እና ዝንጅብል ተጠቃሾች መሆናቸውን ኃላፊው አብራርተዋል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡናን በብዛትና በጥራት ከሚያመረቱ ዞኖች መካከል የቤንች ሸኮ ዞን አንዷ መሆኗም ተገልጿል።
በበጀት ዓመቱ ከ346 ሺህ ኩንታል በላይ ቡናን ለአለም ገቢያ ለማቅርብ እየተሰራ እንደሚገኝ የዞኑ ግብርናና አካባቢ ጥበቃ ህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ጉብላ ተናገረዋል።
ዘጋቢ፦ አብዲሳ ዮናስ ከሚዛን ጣቢያችን።
More Stories
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጅነር አክልሉ አዳኝ ማህበረሰቡን ከቱርካና ሐይቅና ከኦሞ ወንዝ ሙላት ለመከላከል እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በስፍራው በመገኘት ተመለከቱ
የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በየደረጃዉ ለመመለስ እየሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ አስታወቀ
የህዳሴው ግድብ ኢትዮጵያውያን በአንድነት ያሳኩት የጋራ ድል መሆኑን የጨታ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ