ከ346 ሺህ ኩንታል በላይ ቡናን ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅርብ እየተሰራ እንደሚገኝ የቤንች ሸኮ ዞን ግብርናና አካባቢ ጥበቃ ህብረት ሥራ መምሪያ አስታወቀ
በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ ከ35 ሺህ ሄክታር በላይ የቡና ማሳ ያለ ሲሆን ከ25ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ምርት የሚሰጥ መሆኑን የወረዳው ምክትል አስተዳደሪና የግብርናና አካባቢ ጥበቃ ህብረት ሥራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኪዳነ ሽቅ ተናገረዋል።
ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚላከውን የቡና ምርትን ከማሳደግ አኳያ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ በሄክታር
ከ7 እስከ 9 ኩንታል ምርት እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ኪዳኔ በጀንፈል ሲሆን በሄክታር ከ25 እስከ 30 ኩንታል ይገኛል ብለዋል።
በወረዳው በስፋት ከሚመረተው ከቡና ምርት ጎን ለጎን ቅመማ ቅመም ትኩረት ተሰጥተው የሚሰራ ሲሆን ኮረሪማ፣ ቁንዶ በረበሬ፣ ዕረድ እና ዝንጅብል ተጠቃሾች መሆናቸውን ኃላፊው አብራርተዋል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡናን በብዛትና በጥራት ከሚያመረቱ ዞኖች መካከል የቤንች ሸኮ ዞን አንዷ መሆኗም ተገልጿል።
በበጀት ዓመቱ ከ346 ሺህ ኩንታል በላይ ቡናን ለአለም ገቢያ ለማቅርብ እየተሰራ እንደሚገኝ የዞኑ ግብርናና አካባቢ ጥበቃ ህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ጉብላ ተናገረዋል።
ዘጋቢ፦ አብዲሳ ዮናስ ከሚዛን ጣቢያችን።

More Stories
በኢንተርፕራይዝና ኢንቨስትመንት የልማት ስራዎች ላይ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ተገለጸ
በግብርናው ኢኮኖሚ ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ እያስገኘ ያለውን የእንስሳት ሀብት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ነው – የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር መሠረት አበራ
የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን ግብርና መምሪያ ቡናና ቅመማ ቅመም ጽህፈት ቤት አሰታወቀ