በ2016 ዓመተ ምህረት የምርት ዘመን የስንዴ ምርት በምን ያህል ከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ያውቁ ይሆን?
አነስተኛ ማሳ ተጠቃሚ ገበሬዎች 3.6 ሚሊዮን ሄክታር አርሰው 123 ሚሊዮን ኩንታል ሲያመርቱ በመስኖ ከታረሰው 2.9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ደግሞ 107.7 ሚሊዮን ኩንታል ማምረት ተችሏል። የ2016 የኢትዮጵያ የስንዴ ምርት በድምሩ 230 ሚሊዮን ኩንታል ደርሷል።
ከ2012 የምርት ዘመን ጋር ሲነፃፀር አነስተኛ ማሳ ተጠቃሚ ገበሬዎቹ 54 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ብቻ ነበር ያመረቱት። ዛሬ ይህ ቁጥር ትርጉም ባለው መጠን ከፍ ብሏል። ይህ እመርታ በፅኑ አመራር፣ በአስቻይ ፖሊሲዎች ብሎም ምርትን ለማሳደግ በተተገበረ ያላሰለሰ ጥረት የተገኘ ነው። – የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት

More Stories
በያዝነው ዓመት አስከ ጥቅምት ወር ድረስ 2 መቶ 50 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መላኩን የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የምርምር ተቋማት ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የግብርናውን ስራ ውጤታማ እንዲያደርጉ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ስራ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ኢንስቲትዩት አስታወቀ
የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ እና ያለብክነት ሊሰበሰብ እንደሚገባ የባኮ ዳውላ ኣሪ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አሳሰበ