በ2016 ዓመተ ምህረት የምርት ዘመን የስንዴ ምርት በምን ያህል ከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ያውቁ ይሆን?
አነስተኛ ማሳ ተጠቃሚ ገበሬዎች 3.6 ሚሊዮን ሄክታር አርሰው 123 ሚሊዮን ኩንታል ሲያመርቱ በመስኖ ከታረሰው 2.9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ደግሞ 107.7 ሚሊዮን ኩንታል ማምረት ተችሏል። የ2016 የኢትዮጵያ የስንዴ ምርት በድምሩ 230 ሚሊዮን ኩንታል ደርሷል።
ከ2012 የምርት ዘመን ጋር ሲነፃፀር አነስተኛ ማሳ ተጠቃሚ ገበሬዎቹ 54 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ብቻ ነበር ያመረቱት። ዛሬ ይህ ቁጥር ትርጉም ባለው መጠን ከፍ ብሏል። ይህ እመርታ በፅኑ አመራር፣ በአስቻይ ፖሊሲዎች ብሎም ምርትን ለማሳደግ በተተገበረ ያላሰለሰ ጥረት የተገኘ ነው። – የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በማር ምርት ዘርፍ 360 ሺህ ሥራ አጥ ወጣቶችን በማደራጀት ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሠራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ አስታወቁ
በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ ለ2መቶ 50 ድጋፍ ለሚሹ አቅመ-ደካማና አረጋውያን ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር ተደረገ
በበዓላት ሰሞን የትራንስፖርት እጥረት፣ የታሪፍ ጭማሪና የትራፊክ አደጋ እንዳይከሰት እየሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን መንገድና ትራንስፖርት መምሪያ ገለፀ