ከ360 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገዙ የላብራቶሪ ዕቃዎች ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጋቸው ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 09/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ የሳውላ ካምፓስ ከ360 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገዙ የላቮራቶሪ ዕቃዎችን ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጋቸው ተመላከተ።
በካምፓሱ የትምህርት ጥራት ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል።
በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የሳውላ ካምፓስ ኃላፊ አቶ ገብረመድህን ጫመኖ እንደገለጹት፥ ካምፓሱ በሁለት ኮሌጆችና በአንድ የትምህርት ክፍል ከ30 በላይ የትምህርት ፕሮግራም በመጀመሪያና በሁለተኛ ድግሪ በማስተማር ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ካምፓሱ በቴክኖሎጁ ዘርፍ የሚታይበትን የቁሳቁስ ዕጥረት ለመቅረፍ ከ360 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገዙ የላራብራቶሪ ዕቃዎች ለተማሪዎች አገልግሎት እንዲሰጡ ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል።
ያደጉና የበለጸጉ ሀገራት መነሻቸው በትምህርት ዘርፉ ላይ ትኩረት ሰጥተው በመስራታቸው መሆኑን ያነሱት አቶ ገብረመድህን፥ በካምፓሱ የላብራቶሪ የቤተ-መጽሐፍትና የኢንተርኔት ክፍሎች ጥራትና አገልግሎት አሰጣጥ ዘመኑን በሚመጥን ደረጃ የውስጥ አደረጃጀቱን በማጠናከር ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ዩኒቨርሲቲው ካሰለጠናቸው ተማሪዎች በትላልቅ አገራዊ ፕሮጀክቶች የሚቀጠሩ ተመራቂዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።
መምህር ደረስ ዱማዬ እና መምህር መሪሁን ታፈሰ በሰጡት አስተያዬት ተማሪዎች ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በአርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ ዘርፍ በዲጅታል የትምህርት አሰጣጥ ላይ ማተኮራቸውን አስረድተዋል።
ካነጋገርናቸው የካምፓሱ ተማሪዎች መካከል ተማሪ ቢንያም ዳኛቸው እና ተማሪ ጽዮን ታምራት በሰጡት አስተያየት በትምህርታቸው ውጤታማ ለመሆን የጊዜ አጠቃቀማቸውን በፕሮግራም በማድረግና ትምህርታቸው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ከሚፈጥሩ ድርጊቶች ለመታቀብ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል::
ተማሪ ብረሃን ገብሬ እና ተማሪ ኤሊያስ ሽፈራው በበኩላቸው የቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸውን በማሻሻል ተመርቀው ሲወጡ ስራ ፈጣሪ ዜጋ ለመሆን ከወዲሁ ራሳቸውን እያዘጋጁ ስለመሆናቸው አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ አይናለም ሰለሞን – ከሳውላ ጣቢያችን
More Stories
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት ከ2 ሺህ 291 ኪሎ ሜትር በላይ የጠጠር መንገድ እና 112 ድልድዮች ይገነባሉ
የዘንድሮው የሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ “ያሆዴ” በዓል ሲከበር የተቸገሩትን በመደገፍ፣ በመተሳሰብ እና ያለውን ተካፍሎ በመብላት ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የዋቸሞ ዩንቨርስቲ አዲሱን ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 50 ቤተሰቦች ለበዓል መዋያ የሚሆን እህልና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ