ከተለያዩ ሀገር አቀፍ የሚዲያ ተቋማት የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች በቡርጂ ዞን በክላስተር እየለማ ያለውን ጤፍ ጎበኙ
ለ19ኛ ጊዜ በደቡብ የኢትዮጵያ ክልል የሚከበረውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል አከባበር አስመልክቶ ከተለያዩ ሀገር አቀፍ የሚዲያ ተቋማት የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ቡድን በቡርጂ ዞን በክላስተር እየለማ ያለውን የጤፍ ምርት ጎብኝተዋል።
ቡድኑ ወደ ቡርጂ ሲገባ የዞኑ እና የሶያማ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በሶያማ ዙሪያ ወረዳ ነደሌ ቀበሌ የሚገኘውን የክላስተር ጤፍ ሰብል ነው የጎበኙት።
የጉብኝቱ አላማም በደቡብ ክልል በሚገኙ ዞኖች ያለውን እምቅ ሀብት ለሀገር ብሎም ለአለም ማስተዋወቅ ሲሆን ፣በቡርጂ ዞንም በጤፍ ምርት በቂ ምርት እንዳለ ለማየት ተችሏል።
የሚድያ አባላቱ ባዩት የጤፍ ምርት እጅግ መደመማቸውን የገለፁ ሲሆን ኢትዮጵያ በምግብ ሰብል እራሷን ለመቻል እያደረገችው ያለውን ጥረት ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል።
የጉብኝቱ አስተባባሪ የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘላለም ገነሞ የክልል እና ፌደረሽን ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የሚድያ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል ።
ዘጋቢ ፡ ወርቅአገኘሁ ወልደየስ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የቡና ልማትና ግብይትን አስመልክተው የሚወጡ ዓለም-አቀፍ ህጎችን አክብሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው የጥቁር ህዝቦች ኩራት ነው – የኮሬ ዞን አስተዳደር
ግድባችን የአባይ ዘመን ትውልድ ትክክለኛ ሀሳብ፣ በትክክለኛ ጊዜ የገነባነው ዘመን ተሻጋሪ ቅርሳችን ነው ሲሉ በደቡብ ኦሞ ዞን የበና ፀማይ ወረዳ ነዋሪዎች ገለፁ