ከተለያዩ ሀገር አቀፍ የሚዲያ ተቋማት የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች በቡርጂ ዞን በክላስተር እየለማ ያለውን ጤፍ ጎበኙ
ለ19ኛ ጊዜ በደቡብ የኢትዮጵያ ክልል የሚከበረውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል አከባበር አስመልክቶ ከተለያዩ ሀገር አቀፍ የሚዲያ ተቋማት የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ቡድን በቡርጂ ዞን በክላስተር እየለማ ያለውን የጤፍ ምርት ጎብኝተዋል።
ቡድኑ ወደ ቡርጂ ሲገባ የዞኑ እና የሶያማ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በሶያማ ዙሪያ ወረዳ ነደሌ ቀበሌ የሚገኘውን የክላስተር ጤፍ ሰብል ነው የጎበኙት።
የጉብኝቱ አላማም በደቡብ ክልል በሚገኙ ዞኖች ያለውን እምቅ ሀብት ለሀገር ብሎም ለአለም ማስተዋወቅ ሲሆን ፣በቡርጂ ዞንም በጤፍ ምርት በቂ ምርት እንዳለ ለማየት ተችሏል።
የሚድያ አባላቱ ባዩት የጤፍ ምርት እጅግ መደመማቸውን የገለፁ ሲሆን ኢትዮጵያ በምግብ ሰብል እራሷን ለመቻል እያደረገችው ያለውን ጥረት ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል።
የጉብኝቱ አስተባባሪ የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘላለም ገነሞ የክልል እና ፌደረሽን ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የሚድያ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል ።
ዘጋቢ ፡ ወርቅአገኘሁ ወልደየስ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ማሳቸውን ለመኸር እርሻ ደጋግማው በማረስ አለስልሰው በወቅቱ ለመዝራት መዘጋጀታቸውን በከምባታ ዞን ቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ያነጋገርናቸው አንዳንድ አርሶአደሮች ተናገሩ
በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ የስራ ዘርፎች ከ40 ሺህ በላይ ወጣቶችን ተሳታፊ በማድረግ 46 ሚሊዮን 620 ሺህ ብር በላይ ከመንግሥት ሊወጣ የሚችለውን ለማዳን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አስታወቀ
የቀቤና ልዩ ወረዳ ማህበረሰብ የልማት ፍላጎት ማሟላት የሚቻለው ግብርና ታክስ በታማኝነትና በወቅቱ መክፈል ሲቻል መሆኑ ተገለጸ