ከተለያዩ ሀገር አቀፍ የሚዲያ ተቋማት የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች በቡርጂ ዞን በክላስተር እየለማ ያለውን ጤፍ ጎበኙ
ለ19ኛ ጊዜ በደቡብ የኢትዮጵያ ክልል የሚከበረውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል አከባበር አስመልክቶ ከተለያዩ ሀገር አቀፍ የሚዲያ ተቋማት የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ቡድን በቡርጂ ዞን በክላስተር እየለማ ያለውን የጤፍ ምርት ጎብኝተዋል።
ቡድኑ ወደ ቡርጂ ሲገባ የዞኑ እና የሶያማ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በሶያማ ዙሪያ ወረዳ ነደሌ ቀበሌ የሚገኘውን የክላስተር ጤፍ ሰብል ነው የጎበኙት።
የጉብኝቱ አላማም በደቡብ ክልል በሚገኙ ዞኖች ያለውን እምቅ ሀብት ለሀገር ብሎም ለአለም ማስተዋወቅ ሲሆን ፣በቡርጂ ዞንም በጤፍ ምርት በቂ ምርት እንዳለ ለማየት ተችሏል።
የሚድያ አባላቱ ባዩት የጤፍ ምርት እጅግ መደመማቸውን የገለፁ ሲሆን ኢትዮጵያ በምግብ ሰብል እራሷን ለመቻል እያደረገችው ያለውን ጥረት ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል።
የጉብኝቱ አስተባባሪ የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘላለም ገነሞ የክልል እና ፌደረሽን ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የሚድያ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል ።
ዘጋቢ ፡ ወርቅአገኘሁ ወልደየስ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተመራ የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲና የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ቡድን በሰሜን ኣሪ ወረዳ በመገኘት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ተግባራትን መረቀ
ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው የጂንካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት የተጠርጣሪ ማቆያና የቢሮ ህንጻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው በተገኙበት በደማቅ ሥነ ስርዓት በይፋ ተመረቀ
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ1 ቢሊዮን 4 መቶ 21 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የጎፋ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ