ዞኑ በግማሽ ዓመቱ 1 ሺህ 3 መቶ 25 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ አቀረበ
ሀዋሳ፣ መጋቢት 08/2018 (ደሬቴድ) በኮሬ ዞን 1 ሺህ 3 መቶ 25 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ የግማሽ ዓመት አፈጻጸሙን መቶ በመቶ ማሳካት እንደተቻለ ተገልጿል፡፡
የኮሬ ዞን ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጃሌ በ2018 በጀት ዓመት በዞኑ 2 ሺህ 9 መቶ 30 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እንደነበር ገልፀው በግማሽ ዓመት አፈጻጸም 1ሺህ 3 መቶ 25 ነጥብ 4 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡
በዞኑ ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ለመሸፈን ታቅዶ እየተሠራ እንደሚገኝም ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
አክለውም በዞኑ የቡና ማሣ ሽፋን ከ19 ሺህ 6 መቶ 79 ሄክታር በላይ መሆኑን ገልፀው ከ2 ሚሊዮን 9 መቶ ሺህ በላይ አዲስ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሮች ለማሰራጨት ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን አመልክተዋል፡፡
ለቡና እንክብካቤ ከማድረግ፣ ያረጁ ቡናዎችን በአዲስ ከመተካት፣ በኩታ-ገጠም ከመትከልና በጥራት ከማምረት አኳያ ጉድለቶች እንደሚታዩ የገለፁት ኃላፊው እኚህን ችግሮች ለመቅረፍበ ትኩረት እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል ።
የኮሬ ቡና በዓለም አቀፍ ገበያ የሚፈለግ የቡና ዝርያ በመሆኑ ለዓለም ገበያ በሚመጥን መልኩ በጥራት ማምረት አንደሚገባ ገልጸዋል።
ዘጋቢ ፦ ባዩሽ ኢሳያስ- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸዉ ተገለፀ
በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የአርባ ምንጭ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ፣ የአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን አርባ ምንጭ ቅርንጫፍ በጋራ በመሆን ከ300 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የዓይነት ድጋፍ አደረጉ
የማህበረሰቡን የፍትህ ጥማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ እንዲያገኙ ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ