ዞኑ በግማሽ ዓመቱ 1 ሺህ 3 መቶ 25 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ አቀረበ
ሀዋሳ፣ መጋቢት 08/2018 (ደሬቴድ) በኮሬ ዞን 1 ሺህ 3 መቶ 25 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ የግማሽ ዓመት አፈጻጸሙን መቶ በመቶ ማሳካት እንደተቻለ ተገልጿል፡፡
የኮሬ ዞን ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጃሌ በ2018 በጀት ዓመት በዞኑ 2 ሺህ 9 መቶ 30 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እንደነበር ገልፀው በግማሽ ዓመት አፈጻጸም 1ሺህ 3 መቶ 25 ነጥብ 4 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡
በዞኑ ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ለመሸፈን ታቅዶ እየተሠራ እንደሚገኝም ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
አክለውም በዞኑ የቡና ማሣ ሽፋን ከ19 ሺህ 6 መቶ 79 ሄክታር በላይ መሆኑን ገልፀው ከ2 ሚሊዮን 9 መቶ ሺህ በላይ አዲስ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሮች ለማሰራጨት ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን አመልክተዋል፡፡
ለቡና እንክብካቤ ከማድረግ፣ ያረጁ ቡናዎችን በአዲስ ከመተካት፣ በኩታ-ገጠም ከመትከልና በጥራት ከማምረት አኳያ ጉድለቶች እንደሚታዩ የገለፁት ኃላፊው እኚህን ችግሮች ለመቅረፍበ ትኩረት እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል ።
የኮሬ ቡና በዓለም አቀፍ ገበያ የሚፈለግ የቡና ዝርያ በመሆኑ ለዓለም ገበያ በሚመጥን መልኩ በጥራት ማምረት አንደሚገባ ገልጸዋል።
ዘጋቢ ፦ ባዩሽ ኢሳያስ- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ