ዞኑ በግማሽ ዓመቱ 1 ሺህ 3 መቶ 25 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ አቀረበ
ሀዋሳ፣ መጋቢት 08/2018 (ደሬቴድ) በኮሬ ዞን 1 ሺህ 3 መቶ 25 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ የግማሽ ዓመት አፈጻጸሙን መቶ በመቶ ማሳካት እንደተቻለ ተገልጿል፡፡
የኮሬ ዞን ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጃሌ በ2018 በጀት ዓመት በዞኑ 2 ሺህ 9 መቶ 30 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እንደነበር ገልፀው በግማሽ ዓመት አፈጻጸም 1ሺህ 3 መቶ 25 ነጥብ 4 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡
በዞኑ ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ለመሸፈን ታቅዶ እየተሠራ እንደሚገኝም ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
አክለውም በዞኑ የቡና ማሣ ሽፋን ከ19 ሺህ 6 መቶ 79 ሄክታር በላይ መሆኑን ገልፀው ከ2 ሚሊዮን 9 መቶ ሺህ በላይ አዲስ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሮች ለማሰራጨት ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን አመልክተዋል፡፡
ለቡና እንክብካቤ ከማድረግ፣ ያረጁ ቡናዎችን በአዲስ ከመተካት፣ በኩታ-ገጠም ከመትከልና በጥራት ከማምረት አኳያ ጉድለቶች እንደሚታዩ የገለፁት ኃላፊው እኚህን ችግሮች ለመቅረፍበ ትኩረት እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል ።
የኮሬ ቡና በዓለም አቀፍ ገበያ የሚፈለግ የቡና ዝርያ በመሆኑ ለዓለም ገበያ በሚመጥን መልኩ በጥራት ማምረት አንደሚገባ ገልጸዋል።
ዘጋቢ ፦ ባዩሽ ኢሳያስ- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ