ሮድሪጎ ቤንታንኩር ከእግር ኳስ ጨዋታዎች ታገደ
የቶትንሃሙ የመሐል ስፍራ ተጫዋች የሆነው ሮድሪጎ ቤንታንኩር በቡድን አጋሩ ሰን ሁን እና ቤተሰቦቹ ላይ በሰጠው አስተያየት ምክንያት በ7 የእግር ኳስ ጨዋታዎች እገዳ በእንግሊዝ እግርኳስ ማህበር ተጥሎበታል።
ተጫዋቹ ባለፈው መስከረም ወር ላይ በሀገሩ ኡራጓይ ከአንድ መገናኛ ብዙሃን ጋር በነበረው ቃለ መጠይቅ ደቡብ ኮሪያዊው ሰን ሁንግ ሚን እና ቤተሰቦቹ አይናቸውን ጨምሮ ሁሉም ተመሳሳይ ናቸው የሚል አስተያየት መስጠቱን ተከትሎ በእንግሊዝ እግር ኳስ ማህበር ክስ ተከፍቶበት እንደነበረ አይዘነጋም።
የእግር ኳስ ማህበሩ ከጨዋታ ቅጣት በተጨማሪ የ100 ሺህ ፓውንድ የገንዘብ ቅጣት በ27 ዓመቱ ተጫዋች መጣሉን አሳውቋል።
በዚህም መሰረት ሮድሪጎ ቤንታንኩር በፕሪሚዬርሊጉ ክለቡ ከማንቸስተር ሲቲ፣ ሊቨርፑል እና ቼልሲ እንዲሁም በሊግ ካፕ ሩብ ፍፃሜ ከማንቸስተር ዩናይትድ ጋር የሚካሄደው ጨዋታ የሚያመልጠው ይሆናል።
በሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል