ቼልሲ ሌስተርን አሸነፈ
በ12ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬርሊግ ከሜዳው ውጪ ሌስተር ሲቲን የገጠመው ቼልሲ 2ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
የቼልሲን የድል ግቦች ኒኮላስ ጃክሰን እና ኤንዞ ፈርናንዴዝ ከመረብ አሳርፈዋል።
ሌስተርን ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ ጆርዳን አየው በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።
ኒኮላስ ጃክሰን በውድድር ዓመቱ 7ኛ የሊግ ጎሉን ማስቆጠር ችሏል።
ውጤቱን ተከትሎ ቼልሲ ነጥቡን ወደ 22 ከፍ በማድረግ 3ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ሌስተር ሲቲ በ10 ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ፕሪሚዬርሊጉ መካሄዱን ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ አርሰናል ከኖቲንግሃም ፎረስት፣አስቶንቪላ ከክርስቲያል ፓላስ፣በርንማውዝ ከብራይተን፣ ኤቨርተን ከብሬንትፎርድ እና ፉልሃም ከዎልቭስ ይጫወታሉ።
እንዲሁም ምሽት 2ሰዓት ከ30 ደቂቃ ላይ በሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ ማንቸስተር ሲቲ በሜዳው ቶትንሃምን ያስተናግዳል።
በሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት