ፖርቹጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ የእግርኳስ ክለብ ድርሻ ባለቤት መሆኑን አሳውቋል።
የአምስት ጊዜ የባሎንዲኦር አሸናፊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ የስፔኑ ክለብ አልሜሪያ 25 በመቶ ድርሻ መግዛቱ ይፋ ሆኗል።
ክለቡ አሁን ላይ በሳውዲ አረቢያ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ባለቤትነት ተይዞ በመተዳደር ላይ ይገኛል።
በፈረንጆቹ 1989 የተመሰረተው አልሜሪያ በስፔን ሁለተኛ የሊግ ዕርከን እየተወዳደረ የሚገኝ ሲሆን ከመሪው ሪያል ሬሲንግ በሁለት ነጥቦች አንሶ 3ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ከሁለት ዓመት በፊት ነበር ከላሊጋው ወደ ሴጉንዳ ዲቪዚዮኑ የወረደው።
የ41 ዓመቱ ተጫዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ በስፔን በስኬት ታጅቦ ስኬታማ ዘጠኝ ዓመታትን ማሳለፉ ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አትሌት ቢኒያም መላክ እና ውድነሽ ዓለሙ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የጎዳና ሩጫ ውድድርን አሸነፉ
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የምስረታ በዓል የጎዳና ሩጫ ውድድር በሀዋሳ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው
ማርከስ ራሽፎርድ ጉዳት አጋጥሞታል