በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጲያ ህዝቦች ክልል ከ16 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ስራ ላይ ናቸው
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጲያ ህዝቦች ክልል ከ260 በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸውን የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ
የቢሮ ሃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ እንደተናገሩት መንግሰስት በኢንቨስትመንት ዘርፉ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ ይገኛል ብለዋል፡፡
በክልሉ ኢንቨስትመንትን የማነቃቃት ስራዎች በስፋት በመከናወናቸው ቀደም ሲል ከነበሩ 655 ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በለፉት 3 ዓመታት ብቻ 263 አዳዲስ ፕሮጀክቶች ከ16 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል አስመዝግቦ ወደ ስራ መግባታቸውን ገልፀዋል፡፡
ፕሮጀክቶቹ ለ1ሺህ 500 ቋሚና ከ90ሺህ ለሚበልጡ ዜጋዎች ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።
በዘረፉ ፈጥኖ ወደ ስራ የገቡትን ባለሃብቶችን የመበረታታትና የመደገፍ ስራ መሰራቱንም ጠቁመዋል፡፡
በአንጻሩ በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ወደ ስራ ያልገቡ 12 ባለሃብቶች መኖራቸውን አቶ ተመስገን ገልጸው ለእንዚህ ባለሃብቶች የተላለፈ 18ሺህ ሄክታር መሬት በማስመለስ ወደ መረት ባንክ ማስገባት መቻሉንም ገልፀዋል
ዘጋቢ ፡ በየነ ወርቁ ከሚዛን ቅርንጫፍ

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተመራ የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲና የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ቡድን በሰሜን ኣሪ ወረዳ በመገኘት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ተግባራትን መረቀ
ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው የጂንካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት የተጠርጣሪ ማቆያና የቢሮ ህንጻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው በተገኙበት በደማቅ ሥነ ስርዓት በይፋ ተመረቀ
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ1 ቢሊዮን 4 መቶ 21 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የጎፋ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ