በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጲያ ህዝቦች ክልል ከ16 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ስራ ላይ ናቸው
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጲያ ህዝቦች ክልል ከ260 በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸውን የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ
የቢሮ ሃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ እንደተናገሩት መንግሰስት በኢንቨስትመንት ዘርፉ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ ይገኛል ብለዋል፡፡
በክልሉ ኢንቨስትመንትን የማነቃቃት ስራዎች በስፋት በመከናወናቸው ቀደም ሲል ከነበሩ 655 ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በለፉት 3 ዓመታት ብቻ 263 አዳዲስ ፕሮጀክቶች ከ16 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል አስመዝግቦ ወደ ስራ መግባታቸውን ገልፀዋል፡፡
ፕሮጀክቶቹ ለ1ሺህ 500 ቋሚና ከ90ሺህ ለሚበልጡ ዜጋዎች ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።
በዘረፉ ፈጥኖ ወደ ስራ የገቡትን ባለሃብቶችን የመበረታታትና የመደገፍ ስራ መሰራቱንም ጠቁመዋል፡፡
በአንጻሩ በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ወደ ስራ ያልገቡ 12 ባለሃብቶች መኖራቸውን አቶ ተመስገን ገልጸው ለእንዚህ ባለሃብቶች የተላለፈ 18ሺህ ሄክታር መሬት በማስመለስ ወደ መረት ባንክ ማስገባት መቻሉንም ገልፀዋል
ዘጋቢ ፡ በየነ ወርቁ ከሚዛን ቅርንጫፍ

More Stories
ግብር ለአንድ ሀገር ህልውና መረጋገጥ እና ህብረተሰቡ ለሚያነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ወሳኝ በመሆኑ በአሰባሰብ ወቅት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በሀዲያ ዞን የሌሞ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በሩብ ዓመቱ 3.7 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወሰነች ቶማስ ገለጹ
የማር ምርት እጅግ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በጎምቦራ ወረዳ በንብ ማነብ ስራ የተሠማሩ አርሶአደሮች ተናገሩ