በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጲያ ህዝቦች ክልል ከ16 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ስራ ላይ ናቸው
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጲያ ህዝቦች ክልል ከ260 በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸውን የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ
የቢሮ ሃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ እንደተናገሩት መንግሰስት በኢንቨስትመንት ዘርፉ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ ይገኛል ብለዋል፡፡
በክልሉ ኢንቨስትመንትን የማነቃቃት ስራዎች በስፋት በመከናወናቸው ቀደም ሲል ከነበሩ 655 ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በለፉት 3 ዓመታት ብቻ 263 አዳዲስ ፕሮጀክቶች ከ16 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል አስመዝግቦ ወደ ስራ መግባታቸውን ገልፀዋል፡፡
ፕሮጀክቶቹ ለ1ሺህ 500 ቋሚና ከ90ሺህ ለሚበልጡ ዜጋዎች ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።
በዘረፉ ፈጥኖ ወደ ስራ የገቡትን ባለሃብቶችን የመበረታታትና የመደገፍ ስራ መሰራቱንም ጠቁመዋል፡፡
በአንጻሩ በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ወደ ስራ ያልገቡ 12 ባለሃብቶች መኖራቸውን አቶ ተመስገን ገልጸው ለእንዚህ ባለሃብቶች የተላለፈ 18ሺህ ሄክታር መሬት በማስመለስ ወደ መረት ባንክ ማስገባት መቻሉንም ገልፀዋል
ዘጋቢ ፡ በየነ ወርቁ ከሚዛን ቅርንጫፍ

More Stories
የሚተከሉ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ መርሐ ግብሮች የአየር ሚዛንን ከማስጠበቅ ባሻገር በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተገለጸ
በክልሉ 295 የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመለየት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን ግብርና መምሪያ አስተባባሪነት የ2018 ዓ.ም የመኸር ወቅት የተቀናጀ የግብርና ስራዎች ንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል