ተጠባቂው የኤልክላሲኮ ደርቢ በባርሴሎና አሸናፊነት ተጠናቀቀ
በስፔን ላሊጋ 11ኛ ሳምንት በሪያል ማድሪድ እና ባርሴሎና መኻከል የተካሄደው የኤልክላሲኮ ደርቢ በባርሴሎና 4ለ0 አሸናፊነት ተጠናቋል።
ለባርሴሎና ከዕረፍት መልስ የተገኙትን የማሸነፊያ ግቦች ሮበርት ሊቫንዶውስኪ ሁለት ሲያስቆጥር ላሚን ያማል እና ራፊንያ ቀሪ ግቦችን ከመረብ አሳርፈዋል።
ሮበርት ሊቫንዶውስኪ በላሊጋው ያስቆጠራቸውን ግቦች 14 አድርሷል።
ላሚን ያማል በበኩሉ በኤልክላሲኮ የመጀመሪያ ግቡን አስቆጥሯል።
በውድድር ዓመቱ 10ኛ ድሉን ያሳካው ባርሴሎና ነጥቡን 30 በማድረስ መሪነቱን አጠናክሯል።
ሪያል ማድሪድ በላሊጋው ከ42 ጨዋታዎች በኋላ ያለመሸነፍ ጉዞው በብሉግራናዎቹ ተገቷል።
በሙሉቀን ባሳ
More Stories
ስፖርት የወንድማማችነት እና የልማት መጠናከር አንዱ ማሳያ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ
የሀገሪቱን ቦክስ ስፖርት ለማሳደግ የቀድሞ ቦክሰኞችና ሌሎችም አስተዋጽዋቸውን አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ ጥሪ ቀረበ
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው