ተጠባቂው የኤልክላሲኮ ደርቢ በባርሴሎና አሸናፊነት ተጠናቀቀ
በስፔን ላሊጋ 11ኛ ሳምንት በሪያል ማድሪድ እና ባርሴሎና መኻከል የተካሄደው የኤልክላሲኮ ደርቢ በባርሴሎና 4ለ0 አሸናፊነት ተጠናቋል።
ለባርሴሎና ከዕረፍት መልስ የተገኙትን የማሸነፊያ ግቦች ሮበርት ሊቫንዶውስኪ ሁለት ሲያስቆጥር ላሚን ያማል እና ራፊንያ ቀሪ ግቦችን ከመረብ አሳርፈዋል።
ሮበርት ሊቫንዶውስኪ በላሊጋው ያስቆጠራቸውን ግቦች 14 አድርሷል።
ላሚን ያማል በበኩሉ በኤልክላሲኮ የመጀመሪያ ግቡን አስቆጥሯል።
በውድድር ዓመቱ 10ኛ ድሉን ያሳካው ባርሴሎና ነጥቡን 30 በማድረስ መሪነቱን አጠናክሯል።
ሪያል ማድሪድ በላሊጋው ከ42 ጨዋታዎች በኋላ ያለመሸነፍ ጉዞው በብሉግራናዎቹ ተገቷል።
በሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል