ተጠባቂው የኤልክላሲኮ ደርቢ በባርሴሎና አሸናፊነት ተጠናቀቀ
በስፔን ላሊጋ 11ኛ ሳምንት በሪያል ማድሪድ እና ባርሴሎና መኻከል የተካሄደው የኤልክላሲኮ ደርቢ በባርሴሎና 4ለ0 አሸናፊነት ተጠናቋል።
ለባርሴሎና ከዕረፍት መልስ የተገኙትን የማሸነፊያ ግቦች ሮበርት ሊቫንዶውስኪ ሁለት ሲያስቆጥር ላሚን ያማል እና ራፊንያ ቀሪ ግቦችን ከመረብ አሳርፈዋል።
ሮበርት ሊቫንዶውስኪ በላሊጋው ያስቆጠራቸውን ግቦች 14 አድርሷል።
ላሚን ያማል በበኩሉ በኤልክላሲኮ የመጀመሪያ ግቡን አስቆጥሯል።
በውድድር ዓመቱ 10ኛ ድሉን ያሳካው ባርሴሎና ነጥቡን 30 በማድረስ መሪነቱን አጠናክሯል።
ሪያል ማድሪድ በላሊጋው ከ42 ጨዋታዎች በኋላ ያለመሸነፍ ጉዞው በብሉግራናዎቹ ተገቷል።
በሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሲዳማ ቡና አቤል ያለውን እና ሱራፌል ዳኛቸውን አስፈረመ
ክርስቲያኖ ሮናልዶ ወደ እግርኳስ ባለቤትነት
አትሌት ቢኒያም መላክ እና ውድነሽ ዓለሙ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የጎዳና ሩጫ ውድድርን አሸነፉ