በጀርመን ፍራንክፈርት በተካሄደ የሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሀዊ ፈይሳ የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል አሸንፋለች።
አትሌቷ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2 ሰዓት ከ17 ደቂቃ ከ25 ሴኮንድ ፈጅቶባታል።
በወንዶች ማራቶን አትሌት ጎሳ አንበሉ 2ኛ እንዲሁም አትሌት ሌንጮ ተስፋዬ 3ኛ በመሆን አጠናቀዋል።
በሌላ በኩል አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቫሌንሽያ በተካሄደ የግማሽ ማራቶን አዲስ የዓለም ክብረወሰን በማስመዝገብ አሸንፏል።
አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ግማሽ ማራቶኑን 57 ደቂቃ ከ30 ሴኮንድ በማጠናቀቅ ነው አዲስ የዓለም ክብረወሰን ያስመዘገበው።
በሴቶች ግማሽ ማራቶን አትሌት ፎቴን ተስፋዬ 2ኛ፣እጅጋየሁ ታዬ 4ኛ እና ፅጌ ገብረሰላማ 5ኛ በመሆን አጠናቀዋል።
በሙሉቀን ባሳ
More Stories
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል
ስፖርት የወንድማማችነት እና የልማት መጠናከር አንዱ ማሳያ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ