በጀርመን ፍራንክፈርት በተካሄደ የሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሀዊ ፈይሳ የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል አሸንፋለች።
አትሌቷ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2 ሰዓት ከ17 ደቂቃ ከ25 ሴኮንድ ፈጅቶባታል።
በወንዶች ማራቶን አትሌት ጎሳ አንበሉ 2ኛ እንዲሁም አትሌት ሌንጮ ተስፋዬ 3ኛ በመሆን አጠናቀዋል።
በሌላ በኩል አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቫሌንሽያ በተካሄደ የግማሽ ማራቶን አዲስ የዓለም ክብረወሰን በማስመዝገብ አሸንፏል።
አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ግማሽ ማራቶኑን 57 ደቂቃ ከ30 ሴኮንድ በማጠናቀቅ ነው አዲስ የዓለም ክብረወሰን ያስመዘገበው።
በሴቶች ግማሽ ማራቶን አትሌት ፎቴን ተስፋዬ 2ኛ፣እጅጋየሁ ታዬ 4ኛ እና ፅጌ ገብረሰላማ 5ኛ በመሆን አጠናቀዋል።
በሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት