‎50ኛው የኢትዮጵያ ሴቶች ቀን (ማርች 8) በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ እየተከበረ ነው።

‎50ኛው የኢትዮጵያ ሴቶች ቀን (ማርች 8) በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ እየተከበረ ነው።

‎በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በመከበር ላይ ነው።

‎በመርሀ ግብሩ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ ፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት ዶክተር ዳዊት ሀዬሶ ፣ የክልሉ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ ታድመዋል።

‎ከዚህ ባሻገር ከፌደራል ከክልል፣ ከዞን የተውጣጡ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሴት አደረጃጀት ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመርሃ ግብሩ ላይ እየተሳተፉ ናቸው።

‎በፓናል ውይይት የሚከበረው ይህ የሴቶች ቀን በዓል በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሴቶችን ጀግንነትና አይበገሬነት የሚያወሱ ሙዚቃዎች ፣እንስቶች በሀገር ግንባታ ላይ ያሳረፉትን አሻራ የሚያስታውሱ ስነ-ግጥሞችና በብሄር ብሔረሰቦች የባህል ዜማዎችና መሠል ደማቅ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው።

‎ዘጋቢ :- አብደላ በድሩ