50ኛው የኢትዮጵያ ሴቶች ቀን (ማርች 8) በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ እየተከበረ ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በመከበር ላይ ነው።
በመርሀ ግብሩ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ ፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት ዶክተር ዳዊት ሀዬሶ ፣ የክልሉ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ ታድመዋል።
ከዚህ ባሻገር ከፌደራል ከክልል፣ ከዞን የተውጣጡ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሴት አደረጃጀት ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመርሃ ግብሩ ላይ እየተሳተፉ ናቸው።
በፓናል ውይይት የሚከበረው ይህ የሴቶች ቀን በዓል በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሴቶችን ጀግንነትና አይበገሬነት የሚያወሱ ሙዚቃዎች ፣እንስቶች በሀገር ግንባታ ላይ ያሳረፉትን አሻራ የሚያስታውሱ ስነ-ግጥሞችና በብሄር ብሔረሰቦች የባህል ዜማዎችና መሠል ደማቅ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው።
ዘጋቢ :- አብደላ በድሩ

More Stories
ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኮረሪማ ምርት እየለማ መሆኑ ተገለጸ
በጎፋ ዞን ከ12 ሺህ በላይ ተማሪዎች ክልላዊ የ6ኛ ክፍል ፈተና እየተሰጠ ነው
የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በመመለስ በኩል ከመንግስት ጥረት ባለፈ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና የጎላ መሆኑን የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ ተናገሩ