የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት የንቅናቄ መድረክ ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ “ክህሎት መር ስራ ዕድል ፈጠራ ለዕመርታዊ ዕድገት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚያካሂደው የንቅናቄ መድረክ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት መካሔድ ጀምሯል።
በመድረኩ በኢንተርፕራይዞች የተሰሩ ስራዎችን የሚዳስስ ቪዲዮ ለዕይታ የሚቀርብ ሲሆን፥ ከዚህ በተጨማሪ የስራ እድል ፈጠራ ሰነድ ላይ ውይይት በማድረግ ርዕሰ መስተዳድሩ ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በንቅናቄው ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣ የቢሮ ሃላፊዎች፣ የዞንና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የመዋቅሩ አመራሮች እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
በሆሣዕና ከተማ የሚገነቡ ሆቴሎች የከተማውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን በሣላማጎ ወረዳ በሌማት ትሩፋት በቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ