የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት የንቅናቄ መድረክ ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ “ክህሎት መር ስራ ዕድል ፈጠራ ለዕመርታዊ ዕድገት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚያካሂደው የንቅናቄ መድረክ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት መካሔድ ጀምሯል።
በመድረኩ በኢንተርፕራይዞች የተሰሩ ስራዎችን የሚዳስስ ቪዲዮ ለዕይታ የሚቀርብ ሲሆን፥ ከዚህ በተጨማሪ የስራ እድል ፈጠራ ሰነድ ላይ ውይይት በማድረግ ርዕሰ መስተዳድሩ ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በንቅናቄው ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣ የቢሮ ሃላፊዎች፣ የዞንና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የመዋቅሩ አመራሮች እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተመራ የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲና የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ቡድን በሰሜን ኣሪ ወረዳ በመገኘት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ተግባራትን መረቀ
ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው የጂንካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት የተጠርጣሪ ማቆያና የቢሮ ህንጻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው በተገኙበት በደማቅ ሥነ ስርዓት በይፋ ተመረቀ
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ1 ቢሊዮን 4 መቶ 21 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የጎፋ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ