የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት የንቅናቄ መድረክ ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ “ክህሎት መር ስራ ዕድል ፈጠራ ለዕመርታዊ ዕድገት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚያካሂደው የንቅናቄ መድረክ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት መካሔድ ጀምሯል።
በመድረኩ በኢንተርፕራይዞች የተሰሩ ስራዎችን የሚዳስስ ቪዲዮ ለዕይታ የሚቀርብ ሲሆን፥ ከዚህ በተጨማሪ የስራ እድል ፈጠራ ሰነድ ላይ ውይይት በማድረግ ርዕሰ መስተዳድሩ ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በንቅናቄው ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣ የቢሮ ሃላፊዎች፣ የዞንና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የመዋቅሩ አመራሮች እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
በኢንተርፕራይዝና ኢንቨስትመንት የልማት ስራዎች ላይ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ተገለጸ
በግብርናው ኢኮኖሚ ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ እያስገኘ ያለውን የእንስሳት ሀብት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ነው – የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር መሠረት አበራ
የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን ግብርና መምሪያ ቡናና ቅመማ ቅመም ጽህፈት ቤት አሰታወቀ