የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት የንቅናቄ መድረክ ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ “ክህሎት መር ስራ ዕድል ፈጠራ ለዕመርታዊ ዕድገት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚያካሂደው የንቅናቄ መድረክ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት መካሔድ ጀምሯል።
በመድረኩ በኢንተርፕራይዞች የተሰሩ ስራዎችን የሚዳስስ ቪዲዮ ለዕይታ የሚቀርብ ሲሆን፥ ከዚህ በተጨማሪ የስራ እድል ፈጠራ ሰነድ ላይ ውይይት በማድረግ ርዕሰ መስተዳድሩ ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በንቅናቄው ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣ የቢሮ ሃላፊዎች፣ የዞንና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የመዋቅሩ አመራሮች እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ
More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከልላዊ የሻይ ችግኝ ተከላ ስራን በካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ አስጀመረ
ሰልጣኞችን ከስራ ጋር ለማስተሳሰር የኢንዱስትሪ ባለቤቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አስታወቀ
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የብልጽግና ችቧችን ነው – አቶ እንዳሻው ሽብሩ