በ5ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ ማንቸስተር ሲቲ እና አርሰናል 2 አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል።
ኤርሊንግ ሃላንድ እና ጆን ስቶንስ የማንቸስተር ሲቲን ጎሎች ሲያስቆጥሩ ሪካርዶ ካላፊዎሪ እና ጋብርኤል ማጋሌሽ ለአርሰናል አስቆጥረዋል።
በጨዋታው የአርሰናሉ ተጫዋች ሊያንድሮ ትሮሳርድ ጨዋታን በማዘግየት በሚል ከዕረፍት በፊት በሁለት ቢጫ (በቀይ ካርድ) ከሜዳ ተወግዷል።
ኤርሊንግ ሃላንድ ለማንቸስተር ሲቲ በ105 ጨዋታዎች 100ኛ ጎሉን ሲያስቆጥር በጥቂት ጨዋታዎች 100 ጎሎችን በማስቆጠር ከክርስቲያኖ ሮናልዶ ጋር ተጋርቷል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ማንቸስተር ሲቲ በአዲሱ የውድድር ዓመት 2ኛ ተከታታይ ሽንፈት አስተናገደ
ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል
ጄሚ ቫርዲ ወደ ጣሊያን ሴሪኣ ሊያቀና ነው