በ5ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ ማንቸስተር ሲቲ እና አርሰናል 2 አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል።
ኤርሊንግ ሃላንድ እና ጆን ስቶንስ የማንቸስተር ሲቲን ጎሎች ሲያስቆጥሩ ሪካርዶ ካላፊዎሪ እና ጋብርኤል ማጋሌሽ ለአርሰናል አስቆጥረዋል።
በጨዋታው የአርሰናሉ ተጫዋች ሊያንድሮ ትሮሳርድ ጨዋታን በማዘግየት በሚል ከዕረፍት በፊት በሁለት ቢጫ (በቀይ ካርድ) ከሜዳ ተወግዷል።
ኤርሊንግ ሃላንድ ለማንቸስተር ሲቲ በ105 ጨዋታዎች 100ኛ ጎሉን ሲያስቆጥር በጥቂት ጨዋታዎች 100 ጎሎችን በማስቆጠር ከክርስቲያኖ ሮናልዶ ጋር ተጋርቷል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 አሸነፈ