ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) እንደ ሀገር በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሃ-ግብር በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ቆረር ቀበሌ እየተከናወነ ነው።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰላሙ አማዶ፣ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘይኔ ቢልካ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማን ጨምሮ የክልል፣ የዞንና ወረዳ አመራሮች እንዲሁም የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ሚፍታህ ጀማል – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ
በክልሉ የተጀመረውን የልማት እና መልካም አስተዳደር ሥራዎችን በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከግጭት የጸዳ አካባቢ ለመፍጠር ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላም እና ፀጥታ ቢሮ አሳሰበ
በዘመናዊ መንገድ ንብ የማነብ ስራ በመጀመር ውጤታማ መሆናቸውን በወላይታ ዞን የዳሞት ወይዴ ወረዳ ወጣቶች ተናገሩ