ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት በሳንኩራ ወረዳ ረግዲና ቆሬ ቀበሌ እየተካሄደ ነው፡፡
በስነ-ስርዓቱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ የክልሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ መንግሥት ዋና ተጠሪ ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ፣ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም በርካታ በስልጤ ዞን የሳንኩራ ወረዳ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ 600 ሚሊየን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደረጃ ደግሞ 5 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ቀን የመትከል መርሃ-ግብር ሚሊዮኖችን በማሳተፍ እየተካሄደ ነው።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ
በክልሉ የተጀመረውን የልማት እና መልካም አስተዳደር ሥራዎችን በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከግጭት የጸዳ አካባቢ ለመፍጠር ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላም እና ፀጥታ ቢሮ አሳሰበ
በዘመናዊ መንገድ ንብ የማነብ ስራ በመጀመር ውጤታማ መሆናቸውን በወላይታ ዞን የዳሞት ወይዴ ወረዳ ወጣቶች ተናገሩ