የመንግስት በጀት ለታለመለት ዓላማ በአግባቡ ሊውል እንደሚገባ ተገለጸ   

የመንግስት በጀት ለታለመለት ዓላማ በአግባቡ ሊውል እንደሚገባ ተገለጸ           

ሀዋሳ፡ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኦሞ ዞን የበና ፀማይ ወረዳ በ4ተኛ ዙር 6ተኛ ዓመት 23ተኛ መደበኛ ጉባኤ ለ2017 የመንግስት ስራ ማስፈጸሚያ 226 ሚሊዮን 843 ሺህ 681 ብር በጀት አጽድቋል፡፡

የበና ፀማይ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ጋልቦ ጉሜ የማህበረሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መንግስት በትኩረት እየሰራ መሆኑን አንስተው፥ የ2017 የፀደቀው በጀት ትኩረት ለሚሹ ዋና ዋና የልማት ግቦች ብቻ ማዋል እንደሚገባ አሳስበዋል።

ዋናው አፈ ጉባኤው አያያዘው እንደገለጹት፥ ልማት ያለ ማህበረሰብ ተሳትፎ ማሳካት እንደማይቻል ጠቁመው፥ በበጀት አመቱ የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ ማህበረሰቡ ለታቀደው የልማት ሥራ የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡

በበጀት አመቱ የምክር ቤቱ አባላት ያነሷቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች በየደረጃው ለመፈታት እንደሚሰራ ያረጋገጡት የበና ፀማይ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዮሐንስ ጋርሾ  በተዋረድ ያሉ የህዝብ ምክር ቤቶች ህዝቡን የማስተባበር ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ምክር ቤቱ ለ2017 በጀት ዓመት ሥራ ማስፈፀሚያ 226 ሚልዮን 843 ሺ 681 ብር አድርጎ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።

ዋና አስተዳዳሪ በተጓደሉ የካቢኔ አባላትና የምክር ቤቱን ቋሚ ኮሚቴ አቅርበው በምክር  በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል፡፡

ዘጋቢ፡ አርሻል አራቦ – ከጂንካ ጣቢያችን