ኖቫክ ጆኮቪች ካርሎስ አልካሬዝን በማሸነፍ በኦሎምፒክ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አገኘ
በፈረንሳይ አስተናጋጅነት በመካሄድ ላይ በሚገኘው 33ኛ የፓሪስ ኦሎምፒክ በተካሄደው የነጠላ የሜዳ ቴኒስ ውድድር ሰርቢያዊው ኖቫክ ጆኮቪች ስፔናዊውን ካርሎስ አልካሬዝን በማሸነፍ በኦሎምፒክ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ ማግኘት ችሏል።
የ24 ጊዜ የግራንድ ስላም አሸናፊው ኖቫክ ጆኮቪች፥ የዓለም ቁጥር ሶስት የሜዳ ቴኒስ ተወዳዳሪውን ካርሎስ አልካሬዝን በሁለቱም ዙሮች 7ለ6 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ነው የወርቅ ሜዳልያው ባለቤት መሆን የቻለው።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት