ኖቫክ ጆኮቪች ካርሎስ አልካሬዝን በማሸነፍ በኦሎምፒክ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አገኘ
በፈረንሳይ አስተናጋጅነት በመካሄድ ላይ በሚገኘው 33ኛ የፓሪስ ኦሎምፒክ በተካሄደው የነጠላ የሜዳ ቴኒስ ውድድር ሰርቢያዊው ኖቫክ ጆኮቪች ስፔናዊውን ካርሎስ አልካሬዝን በማሸነፍ በኦሎምፒክ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ ማግኘት ችሏል።
የ24 ጊዜ የግራንድ ስላም አሸናፊው ኖቫክ ጆኮቪች፥ የዓለም ቁጥር ሶስት የሜዳ ቴኒስ ተወዳዳሪውን ካርሎስ አልካሬዝን በሁለቱም ዙሮች 7ለ6 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ነው የወርቅ ሜዳልያው ባለቤት መሆን የቻለው።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ተጠባቂው የማንቹሪያን ደርቢ አመሻሽ 12 ሰዓት ከ30 ደቂቃ ላይ ይካሄዳል
አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ወደ ፍፃሜ አለፈች
የ10 ሺህ ሜትር ወንዶች የፍፃሜ ውድድር ከደቂቃዎች በኋላ ይካሄዳል