በ800 ሜትር ሴቶች አትሌት ወርቅነሽ መለሰ እና ፅጌ ድጉማ ወደ ፍፃሜው አለፉ
በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ በ800 ሜትር ሴቶች ግማሽ ፍፃሜ የተወዳደሩት አትሌት ወርቅነሽ መለሰ እና አትሌት ፅጌ ድጉማ ወደ ፍፃሜው አልፈዋል።
በመጀመሪያው ምድብ የግማሽ ፍፃሜ ውድድሯን ያከናወነችው አትሌት ወርቅነሽ መሰለ 2ኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ ፍፃሜውን ተቀላቅላለች።
በሁለተኛው ምድብ ወደ ፍፃሜው ለማለፍ የተወዳደረችው አትሌት ፅጌ ድጉማ አንደኛ ሆና ውድድሯን አጠናቃለች።
የሴቶች 800 ሜትር ፍፃሜ ውድድር ነገ ምሽት 4 ሰዓት ከ45 ላይ የሚደረግ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
የሀገሪቱን ቦክስ ስፖርት ለማሳደግ የቀድሞ ቦክሰኞችና ሌሎችም አስተዋጽዋቸውን አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ ጥሪ ቀረበ
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ