በ800 ሜትር ሴቶች አትሌት ወርቅነሽ መለሰ እና ፅጌ ድጉማ ወደ ፍፃሜው አለፉ
በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ በ800 ሜትር ሴቶች ግማሽ ፍፃሜ የተወዳደሩት አትሌት ወርቅነሽ መለሰ እና አትሌት ፅጌ ድጉማ ወደ ፍፃሜው አልፈዋል።
በመጀመሪያው ምድብ የግማሽ ፍፃሜ ውድድሯን ያከናወነችው አትሌት ወርቅነሽ መሰለ 2ኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ ፍፃሜውን ተቀላቅላለች።
በሁለተኛው ምድብ ወደ ፍፃሜው ለማለፍ የተወዳደረችው አትሌት ፅጌ ድጉማ አንደኛ ሆና ውድድሯን አጠናቃለች።
የሴቶች 800 ሜትር ፍፃሜ ውድድር ነገ ምሽት 4 ሰዓት ከ45 ላይ የሚደረግ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል ክርስቶስ ዞሊስን ለማስፈረም ተስማማ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በወልቂጤ ከተማ የሰርከስ ስፖርት ምልመላና የማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት መርሃ ግብር ተካሄደ
አሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል እንግሊዝ ወደ ፍፃሜ ባለማለፏ ከፍተኛ ትችትን አስተናገዱ