የአፍሪካ ዋንጫ ዛሬ ፍፃሜውን ያገኛል

የአፍሪካ ዋንጫ ዛሬ ፍፃሜውን ያገኛል

በኮትዲቯር አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ዛሬ ምሽት 5:00 በሚካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ ይጠናቀቃል።

በድንቅ ብቃት እየገሰገሰች የመጣችው ናይጀሪያ እና በተዓምር እና ዕድል ታጅባ ለዛሬው ቀን የደረሳቸው ኮትዲቯር ይገናኛሉ።

አሁን ባላት ወቅታዊ ብቃት ናይጀሪያ የማሸነፍ ዕድል አላት እየተባለ ቢሆንም ኮትዲቯር በደጋፊዎቿ ታግዛ ዋንጫን በማሸነፍ ሌላ ተዓምር ታሳያለች እያሉ ነው የኳስ አዋቂዎች።

የዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ጥራት እና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እየተካሄደ መሆኑ የበርካቶችን ትኩረት እንዲያኝ አድርጎታል።

ከአንድ ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ ያደረገችው አስተናጋጅ ሀገር ኮትዲቯር ልፋቷ መና እንዳልቀረ በርካቶች እየመሰከሩ ነው።

የዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ በበርካታ ድንገቴዎችና አዳዲስ ክስተቶች መታጀቡ ልዩ መገለጫው ነው፡፡

አዘጋጅ: ጀማል የሱፍ