ኮኬይን የተባለ አደገኛ ዕፅ ውጠው የተገኙ የብራዚልና የኢንዶኔዥያ ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር ዋሉ
ሀዋሳ፡ ጥር 28/2016 ዓ.2016 (ደሬቴድ) ኮኬይን የተባለ አደገኛ ዕፅ ውጠው የተገኙ የብራዚልና የኢንዶኔዥያ ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር ውለዋል።
የአደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪዎቹ ከብራዚልና ከኢንዶኔዥያ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ ፖሊስ ከሲቪል አቪዬሽን ደህንነት ዋና መምሪያ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሴኩሪቲ፣ ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን እና ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር በኤክስሬይ ማሽን በተደረገው ፍተሻ ኮኬይን የተባለ አደገኛ ዕፅ ውጠው ስለተገኙ በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እያጣራባቸው እንደሚገኝ ገልጿል።
በአጠቃላይ የብራዚል ዜግነት ካላት ተጠርጣሪ በእንክብል መልክ የተዘጋጀ 2.900 ኪሎ ግራም ኮኬይን የተያዘ ሲሆን እስከአሁን ሰባት ፍሬ ኮኬይን ደግሞ ከሆዷ መውጣቱን የገለፀው ፖሊስ ሌላው የኢንዶኔዥያ ዜግነት ያለው ተጠርጣሪ ደግሞ ከዋጠው በተጨማሪ 6.70 ኪሎ ግራም በሻንጣ ውስጥ ሰፍቶ ፍተሻውን ለማለፍ ሲሞክር ከነ-ኤግዚቪቱ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው አረጋግጧል።
ምንጭ ፡ ፌዴራል ፖሊስ

More Stories
የሀለባ ዞን ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ3 ቢልዮን 293 ሚልዮን ብር ባለይ በጀት አጸደቀ
መስራት እየቻሉ የገንዘብ እጥረት የገጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን ችግሮች ለመፍታት የህብረት ስራ ማህበራት ሚና ቀላል አለመሆኑ ተገለጸ
በስልጤ ልማት ማህበር ለ3ኛ ጊዜ በተዘጋጀው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ከሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር የተሰበሰቡ የአካባቢው ተወላጆች በዞኑ በሚገኙ የላንፉሮ ወረዳና ጦራ ከተማ አስተዳደር ችግኞችን ተክለዋል ።