ሀዋሳ፡ የካቲት 25/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የፍትህ ስርዓቱን ተደራሽና ቀልጣፋ ለማድረግ የባህልና መደበኛ ፍርድ ቤቶችን አቀናጅቶ እየሰራ መሆኑን የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታወቀ።
የዞኑ ፍርድ ቤቶች የግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማና የመልካም አስተዳደር መድረክ መካሄድ ጀምሯል።
የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ መንግስቱ ከበደ በመድረኩ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፥ በየደረጃው የሚገኙ ፍርድ ቤቶች መልካም አስተዳደርንና ፍትህን ለማስፈን የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛል ብለዋል።
የቀበሌ ማህበራዊ ፍርድ ቤቶችና ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ለፍትህ ተደራሽነት እያበረከቱ ያሉት አስተዋጽዖ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።
መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በየደረጃው በሚገኙ አፈ-ጉባኤዎች የህዝብ አስተያየት የመሰብሰብና ለፍርድ ቤቶች መረጃ የመስጠት ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።
በበጀት አመቱ በወንጀልና ፍታብሔር 11 ሺህ 364 መዝገቦች ቀርበው 9 ሺህ 948 መዝገቦች ላይ ውሳኔ መሰጠቱን ገልጸዋል።
የቀሩት 1 ሺህ 416 መዝገቦች ለቀጣይ በጀት አመት መተላለፋቸውን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ አፈጻሙ 87 በመቶ በላይ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመድረኩ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ጥላሁን ታደመ፣ የካፋ ዞን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አሚናት ሀሰንን ጨምሮ የወረዳና ከተማ አስተዳደሮች ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ነዉ።
ዘጋቢ፡ ባርታ ታዬ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ