ምርጫው ነፃ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሀዊና ተአማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሴቶች ድርሻ የጎላ መሆን አለበት ሲሉ አንዳንድ ያነጋገርናቸው ሴት አመራሮች ገልፀዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ፀሀይ ወራሳ፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ሠላማዊ፣ ፍትሀዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ማካሄድ ዋነኛ ግብ ነው በማለት ምርጫው ስኬታማ እንዲሆን ሴቶች በግንባር ቀደምነት በመሳተፍ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ለሀገር ግንባታና ሠላም የሴቶች ድርሻ የጎላ መሆኑን የ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማሳያ ነው ያሉት ኃላፊዋ፤ ሀገራችን ወደ መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሀገሮች ተርታ እንድትሰለፍና የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን መሥራት ይጠበቅብናል ሲሉም አመላክተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ተስፋነሽ ጥላሁን፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ሠላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የምክር ቤት አባላትና ሴቶች በተገቢው ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል በማለት ሀሳባቸውን ሰንዝረዋል።
የወናጎ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፍሬነሽ ሮባ በበኩላቸው፤ ለምርጫ ሂደት ውጤታማነት በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሴቶች ተሳትፎ የነበሩ ጥንካሬዎችን በመውሰድና ጉድለቶችን በማረም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ በላቀ ደረጃ አጠናክሮ ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።
ዘጋቢ: ፅጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ