ምርጫው ነፃ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሀዊና ተአማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሴቶች ድርሻ የጎላ መሆን አለበት ሲሉ አንዳንድ ያነጋገርናቸው ሴት አመራሮች ገልፀዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ፀሀይ ወራሳ፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ሠላማዊ፣ ፍትሀዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ማካሄድ ዋነኛ ግብ ነው በማለት ምርጫው ስኬታማ እንዲሆን ሴቶች በግንባር ቀደምነት በመሳተፍ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ለሀገር ግንባታና ሠላም የሴቶች ድርሻ የጎላ መሆኑን የ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማሳያ ነው ያሉት ኃላፊዋ፤ ሀገራችን ወደ መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሀገሮች ተርታ እንድትሰለፍና የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን መሥራት ይጠበቅብናል ሲሉም አመላክተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ተስፋነሽ ጥላሁን፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ሠላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የምክር ቤት አባላትና ሴቶች በተገቢው ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል በማለት ሀሳባቸውን ሰንዝረዋል።
የወናጎ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፍሬነሽ ሮባ በበኩላቸው፤ ለምርጫ ሂደት ውጤታማነት በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሴቶች ተሳትፎ የነበሩ ጥንካሬዎችን በመውሰድና ጉድለቶችን በማረም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ በላቀ ደረጃ አጠናክሮ ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።
ዘጋቢ: ፅጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ