በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞን ዲላ ማዕከል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።
የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተዘጋጀ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ በጌዴኦ ዞን ዲላ ማዕከል መካሔድ ጀምሯል።
“የኢትዮጵያን ሠላም አስጠብቃለሁ ለልጆቼ ምንዳን አወርሳለሁ” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ በሚገኘው መድረክ፥ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ሥራ አስፈፃሚ አካላት፣ የክልልና የዞን የሴቶች ሊግ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የወረዳዎች እና ከተማ አስተዳሮች የዘርፉ አመራርና እና አባላት ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ግብር ለአንድ ሀገር ህልውና መረጋገጥ እና ህብረተሰቡ ለሚያነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ወሳኝ በመሆኑ በአሰባሰብ ወቅት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በሀዲያ ዞን የሌሞ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በሩብ ዓመቱ 3.7 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወሰነች ቶማስ ገለጹ
የማር ምርት እጅግ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በጎምቦራ ወረዳ በንብ ማነብ ስራ የተሠማሩ አርሶአደሮች ተናገሩ