በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው

ሀዋሳ፡ ጥር 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞን ዲላ ማዕከል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።

የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተዘጋጀ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ በጌዴኦ ዞን ዲላ ማዕከል መካሔድ ጀምሯል።

“የኢትዮጵያን ሠላም አስጠብቃለሁ ለልጆቼ ምንዳን አወርሳለሁ” በሚል መሪ ቃል  እየተካሄደ በሚገኘው መድረክ፥ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ሥራ አስፈፃሚ አካላት፣ የክልልና የዞን የሴቶች ሊግ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የወረዳዎች እና ከተማ አስተዳሮች የዘርፉ አመራርና እና አባላት ተሳትፈዋል።

ዘጋቢ: አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን