በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞን ዲላ ማዕከል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።
የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተዘጋጀ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ በጌዴኦ ዞን ዲላ ማዕከል መካሔድ ጀምሯል።
“የኢትዮጵያን ሠላም አስጠብቃለሁ ለልጆቼ ምንዳን አወርሳለሁ” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ በሚገኘው መድረክ፥ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ሥራ አስፈፃሚ አካላት፣ የክልልና የዞን የሴቶች ሊግ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የወረዳዎች እና ከተማ አስተዳሮች የዘርፉ አመራርና እና አባላት ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በያዝነው ዓመት አስከ ጥቅምት ወር ድረስ 2 መቶ 50 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መላኩን የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የምርምር ተቋማት ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የግብርናውን ስራ ውጤታማ እንዲያደርጉ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ስራ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ኢንስቲትዩት አስታወቀ
የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ እና ያለብክነት ሊሰበሰብ እንደሚገባ የባኮ ዳውላ ኣሪ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አሳሰበ