በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞን ዲላ ማዕከል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።
የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተዘጋጀ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቀፍ የሠላምና የሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የንቅናቄ መድረክ በጌዴኦ ዞን ዲላ ማዕከል መካሔድ ጀምሯል።
“የኢትዮጵያን ሠላም አስጠብቃለሁ ለልጆቼ ምንዳን አወርሳለሁ” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ በሚገኘው መድረክ፥ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ሥራ አስፈፃሚ አካላት፣ የክልልና የዞን የሴቶች ሊግ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የወረዳዎች እና ከተማ አስተዳሮች የዘርፉ አመራርና እና አባላት ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በሆሣዕና ከተማ የሚገነቡ ሆቴሎች የከተማውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን በሣላማጎ ወረዳ በሌማት ትሩፋት በቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ