የ2016 ተፋሰስ ልማት ማስጀመሪያ መረሃ ግብር በወላይታ ዞን ካዋ ኮይሻ ወረዳ በይፋ ተጀመረ
ሀዋሳ፡ ጥር 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን የ2016 ተፋሰስ ልማት ማስጀመሪያ መረሃ ግብር በዛሬው ዕለት በዞኑ ካዋ ኮይሻ ወረዳ በይፋ መጀመሩ ተጠቁሟል።
በዘንድሮ ተፋሰስ ልማት ከ76 ሽህ ሄክታር መሬት በላይ ለማልማት መታቀዱ ተገልጿል።
በመርሃ ግብሩ ከክልልና ከዞን የተወጣጡ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የአከባቢው ህብረተሰብ፣ የሐይማኖት አባቶቻችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።
እንደ ወላይታ ዞን ከዚህ ቀደም በተሰራው የተፋሰስ ሥራ በአከባቢው የአየር ንብረት ለውጥ ለመቋቋም የሚያስችሉ ውጤቶችን ማምጣት መቻሉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ ተናግረዋል።
በቀጣይም ለአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ትኩረት በመስጠት ለውጤታማነቱ ተግተው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱም 76 ሽህ 9 መቶ 73 ሄክታር መሬት ለማልማት መታቀዱ የተጠቆመ ሲሆን፥ ይህም ለተከታታይ 30 ቀናት በህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚከናወን መሆኑ ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ግብዓቶች አጠቃቀም ማሻሻልና ማዘመን እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
ጥራት ያለው ኮረሪማ ለገበያ ለማቅረብና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ትኩረት መደረጉን የአሪ ዞን ቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የቡና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ገለጹ