የ2016 ተፋሰስ ልማት ማስጀመሪያ መረሃ ግብር በወላይታ ዞን ካዋ ኮይሻ ወረዳ በይፋ ተጀመረ
ሀዋሳ፡ ጥር 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን የ2016 ተፋሰስ ልማት ማስጀመሪያ መረሃ ግብር በዛሬው ዕለት በዞኑ ካዋ ኮይሻ ወረዳ በይፋ መጀመሩ ተጠቁሟል።
በዘንድሮ ተፋሰስ ልማት ከ76 ሽህ ሄክታር መሬት በላይ ለማልማት መታቀዱ ተገልጿል።
በመርሃ ግብሩ ከክልልና ከዞን የተወጣጡ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የአከባቢው ህብረተሰብ፣ የሐይማኖት አባቶቻችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።
እንደ ወላይታ ዞን ከዚህ ቀደም በተሰራው የተፋሰስ ሥራ በአከባቢው የአየር ንብረት ለውጥ ለመቋቋም የሚያስችሉ ውጤቶችን ማምጣት መቻሉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ ተናግረዋል።
በቀጣይም ለአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ትኩረት በመስጠት ለውጤታማነቱ ተግተው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱም 76 ሽህ 9 መቶ 73 ሄክታር መሬት ለማልማት መታቀዱ የተጠቆመ ሲሆን፥ ይህም ለተከታታይ 30 ቀናት በህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚከናወን መሆኑ ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በሆሣዕና ከተማ የሚገነቡ ሆቴሎች የከተማውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን በሣላማጎ ወረዳ በሌማት ትሩፋት በቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ