የአፍሪካ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ይጀመራሉ
የአፍሪካ ሃያላን ብሔራዊ ቡድኖችን በጊዜ ያሰናበተው ሰላሳ አራተኛው የኮትዲቯር አፍሪካ ዋንጫ ሁለት የሩብ ፍጻሜ መርሀግብሮችን ዛሬ ያስተናግዳል።
በዚህም ናይጀሪያ ከ አንጎላ እንዲሁም ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ከ ጊኒ የሚያደርጉት ጨዋታ በሩብ ፍጻሜው ዛሬ የሚጠበቁ መርሀግብሮች ናቸው።
ናይጄሪያ ከ አንጎላ የሚያከናውኑት ጨዋታ፣ ምሽት 2:00 አርባ አምስት ሺህ ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ባለው በስቴድ ፌልክስ ሀውፎኤት ቦይጅኒ ስታዲየም የሚጀመር ይሆናል።
ምሽት 5:00 በስቴድ ኦሎምፒክ አላሳኔ ኦታራ ስታዲየም ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ከ ጊኒ የሚገናኙበት የእለቱ ሁለተኛው መርሀግብር ነው።
ዘጋቢ: ዘላለም ዳዊት

More Stories
“ከማንችስተር ዩናይትድ ልወጣ እችል ነበር፤ ነገር ግን እዚህ ስኬታማ መሆን ትልቅ ትርጉም አለው”ብሩኖ ፈርናንዴዝ
ማንችስተር ዩናይትድ እና አርሰናል ሳንድሮ ቶናሊን ለማስፈረም ፉክክር ጀምረዋል
አሽሊ ያንግ ጫማውን ሰቀለ