የአፍሪካ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ይጀመራሉ
የአፍሪካ ሃያላን ብሔራዊ ቡድኖችን በጊዜ ያሰናበተው ሰላሳ አራተኛው የኮትዲቯር አፍሪካ ዋንጫ ሁለት የሩብ ፍጻሜ መርሀግብሮችን ዛሬ ያስተናግዳል።
በዚህም ናይጀሪያ ከ አንጎላ እንዲሁም ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ከ ጊኒ የሚያደርጉት ጨዋታ በሩብ ፍጻሜው ዛሬ የሚጠበቁ መርሀግብሮች ናቸው።
ናይጄሪያ ከ አንጎላ የሚያከናውኑት ጨዋታ፣ ምሽት 2:00 አርባ አምስት ሺህ ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ባለው በስቴድ ፌልክስ ሀውፎኤት ቦይጅኒ ስታዲየም የሚጀመር ይሆናል።
ምሽት 5:00 በስቴድ ኦሎምፒክ አላሳኔ ኦታራ ስታዲየም ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ከ ጊኒ የሚገናኙበት የእለቱ ሁለተኛው መርሀግብር ነው።
ዘጋቢ: ዘላለም ዳዊት
More Stories
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 አሸነፈ