ዛሬ ምሽት የአፍሪካ ዋንጫ ተጠባቂ ፊልሚያዎችን ያስተናግዳል
ሀዋሳ፡ ጥር 08/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ)የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡ሁሉም ቡድኖች አንድ አንድ ጨዋታ አድርገዋል። ያልተጠበቁ ውጤቶች ፉክክሩን አጓጊ እያደረጉት ነው።
ዛሬ ምሽት እጅግ ተጠባቂ ጨዋታዎችም ይካሄዳሉ ።
አስተናጋጅ ሀገር ኮትድቯር ከናይጄሪያ የሚያደርጉት ከፍተኛ ትንቅንቅ በኳስ አፍቃሪያን ዘንድ በጉጉት እየተጠበቀ ነው።
ሁለቱም ሀገራት አለም አቀፍ ዕውቅና ያላቸው ከዋክብትን መያዛቸው ትኩረት ውስጥ እንዲገቡ አደርጓቸዋል።
በመጀመሪያው ጨዋታቸው ኮትድቯር ጊኒ ቢሳኦን ጊኒን ሁለት ለዜሮ አሸንፋለች ።
ናይጄሪያ ደግሞ ብዙ ተቸግራ ኢኳቶሪያል ጊኒን አንድ ለዜሮ ማሸነፏ ይታወሳል።
ጨዋታው አምስት ሰዓት ጅማሬውን ያደርጋል ።
ጊኒ ቢሳኦና ኢኳቶሪያል ጊኒም ጨወታ አላቸው ።
ዛሬ ምሽት የሚደረገው የጋና እና የግብፅ ፍልሚያም በጉጉት የሚጠበቅ ፉክክር ነው። ሁለቱ ቡድኖች በአፍሪካ ያላቸው ተቀናቃኝነት ተጠባቂ ያደርገዋል።
ጋና በመጀመሪያው ጨዋታ በኬፕቨርዴ ሁለት ለአንድ መሸነፏ የዛሬን ጨዋታ ማሸነፍ ግዴታዋ ይሆናል።
ግብፅ ደግሞ ከሞዛምቢክ ሁለት አቻ ወጥታለች ። በመሆኑም ጋናም ሆነች ግብፅ ከዛሬው ጨዋታ ሙሉ ሶስት ነጥብ ይፈልጋሉ ።
ጨዋታው አምስት ሰዓት ይጀምራል ።
አዘጋጅ : ጀማል የሱፍ
More Stories
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል
ስፖርት የወንድማማችነት እና የልማት መጠናከር አንዱ ማሳያ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ