የበልግ እርሻ ልማት የንቅናቄ መድረክ በሙዱላ ከተማ እየተካሄደ ነው

የበልግ እርሻ ልማት የንቅናቄ መድረክ በሙዱላ ከተማ እየተካሄደ ነው

ሀዋሳ: ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የበልግ እርሻ ልማት የንቅናቄ መድረክ በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ሙዱላ ከተማ እየተካሄደ ነው::

በንቅናቄ መድረኩ ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውን ጨምሮ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና  የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፤ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፤ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ  አኒቶ፤ የግብርና ሚኒስትር ዲኤታ ፕሮፈሰር ኢያሱ ኤልያስና ሌሎችም የክልል፤የዞኖችና እና የልዩ ወረዳው የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል::

ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ