መጪው ጠቅላላ ምርጫ ተአማኒና በህዝቡ ዘንድ ቅቡልነት ያለው እንዲሆን በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ደሣለኝ ገለፁ
የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ ማኒፌስቶ የክልልና የዞን አመራሮች፣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል።
የዞኑ መንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለምብርሃን ካሳሁን፥ ኢትዮጵያ ለዘመናት የገጠሟትን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ስብራቶች በሪፎርም በማከም ጠንካራ ፓርቲና መንግሥት የመገንባት ተልዕኮዋን በብቃት እየተወጣች ትገኛለች ብለዋል።
በኢኮኖሚው ዘርፍ ሀገር በቀል ሪፎርሞችን ተግባራዊ በማድረግ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ከመፍጠር ባለፈ፥ የገበያ ሥርዓቱን ፍትሐዊና ተወዳዳሪ የሚያደርጉ ስልታዊ እርምጃዎች እንደተወሰዱ ገልጸዋል።
ከዲፕሎማሲው ረገድም ከነበረብን ተከልካይ አካሄድ ወጥተን የሀገራችንን ሉዓላዊ ጥቅም የሚያስከብር የጋራ ተጠቃሚነት መርሆን በመከተል ታላላቅ ድሎች መመዝገባቸውን አቶ አለምብርሃን አንስተዋል።
በተለይም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ ኢትዮጵያውያን በአፍሪካ ቀንድ አዲስ ጂኦ-ስትራቴጂያዊ ትርክትና ዳግማዊ የዓድዋ ድል የማስመዝገብ አቅም እንዳለን ለዓለም ያሳየንበት የታሪካችን ወርቃማ ምዕራፍ ሆኗል ብለዋል።
የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ በማዳመጥ በመልማት አማራጮች ላይ ጊዜ ወስዶ በማሰብና በመለየት የአጭር፣ የመካከለኛ እና ረጅም ጊዜ ዕቅድ በማዘጋጀት ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ አመላክተዋል።
ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠልና ለ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት፣ እንደ ብልፅግና ፓርቲና መንግሥት አስቻይ ሁኔታ የመፍጠርና እንደ ተወዳዳሪ ፓርቲ ደግሞ በአሽናፊነት የመውጣት ድርብ ኃላፊነት ይጠብቅብናል ብለዋል።
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ደሳለኝ በበኩላቸው ባለፉት ጊዚያት እንደሐገር የማይደፈሩ የሚመሥሉ ልማታዊ አጀንዳዎችን ፓርቲው ደፍሮ መፈጸም መቻሉንና በቀጣይም እንደሚፈጽም ተናግረዋል።
የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ሰፋፊ የኢኮኖሚ ሪፎርሞች መደረጋቸውን ያነሱት አስተዳዳሪው በገጠርና በከተማ የተያዙ ልማታዊ ኢኒሼቲቭ አጀንዳዎችን አመርቂ ውጤት አስመዝግቧዋል ብለዋል።
ፓርቲው የሚከተለው አካታች የዲሞክራሲ እይታ በአዲስ መልክ በተደራጀው ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባስኬቶ ዞን የፓለቲካዊ ተሳትፎና የልማት ተጠቃሚነት እንየዲጨምር ማስቻሉን ጠቅሰዋል።
የብልፀግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የአብሮነት ተምሳሌት መሆኑን ያብራሩት አስተዳዳሪው ምርጫው በሠላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ጥረት ይደረጋል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ነው
የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 28ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል
ህፃናትን በወቅቱ በማስከተብ ለተለያዩ በሽታዎች እንዳይጋለጡ እየተሰራ መሆኑን በቡርጂ ዞን ሶያማ ከተማ አስተዳደር ጤና ዩኒት ገለጸ