ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው የዘንድሮውን የተፋሰስ ልማት ሥራ በይፋ አስጀመሩ
ሀዋሳ: ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው የዘንድሮውን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ገእቻ ቀበሌ በይፋ አስጀምረዋል::
በማስጀመሪያ መርሀግብር ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውን ጨምሮ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የግብርና ሚኒስትር ዲኤታ ፕሮፌሰር ኢያሱ ኤልያስና ሌሎችም የክልል፣ የዞኖችና እና የልዩ ወረዳው የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ግብዓቶች አጠቃቀም ማሻሻልና ማዘመን እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
ጥራት ያለው ኮረሪማ ለገበያ ለማቅረብና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ትኩረት መደረጉን የአሪ ዞን ቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የቡና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ገለጹ