ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው የዘንድሮውን የተፋሰስ ልማት ሥራ በይፋ አስጀመሩ
ሀዋሳ: ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው የዘንድሮውን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ገእቻ ቀበሌ በይፋ አስጀምረዋል::
በማስጀመሪያ መርሀግብር ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውን ጨምሮ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የግብርና ሚኒስትር ዲኤታ ፕሮፌሰር ኢያሱ ኤልያስና ሌሎችም የክልል፣ የዞኖችና እና የልዩ ወረዳው የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
በያዝነው ዓመት አስከ ጥቅምት ወር ድረስ 2 መቶ 50 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መላኩን የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የምርምር ተቋማት ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የግብርናውን ስራ ውጤታማ እንዲያደርጉ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ስራ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ኢንስቲትዩት አስታወቀ
የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ እና ያለብክነት ሊሰበሰብ እንደሚገባ የባኮ ዳውላ ኣሪ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አሳሰበ