የጌዴኦ ባህላዊ መልከአ ምድር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የዕዉቅና መርሃግብር እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጌዴኦ ባህላዊ መልከአ ምድር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የዕዉቅና መርሃግብር በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ በጨልባ ቱቲቲ የባህል ቅርስ እየተካሄደ ይገኛል።
የጌዴኦ ባህላዊ መልከአ ምድር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስነት መመዝገቡ ይታወሳል።
በዓለም ቅርስነት የተመዘገበዉ የጌዴኦ ባህላዊ መልከዓ ምድር ቅርስ በዉስጡ ከስድስት ሺህ በላይ የሚሆኑ ትክል ድንጋይ እና ጥምር ደን እርሻ ይገኙበታል።
በህብረተሰቡ ፍላጎት የተሰራና ባህሉን እሴቱን በማኖሮ እያለማ ጠብቆ ያቆየው ባህላዊ መልከዓ ምድር ቅርስ ነው።
በዕዉቅና አሰጣጥ መርሃ ግብሩ ላይ የፌደራል፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ፍሬህይወት ዱባለ፣ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘውዱ

More Stories
የፍትህ ስርዓቱን ተደራሽና ቀልጣፋ ለማድረግ እየተሰራ ነዉ – የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን ሴቶች በግንባር ቀደምነት በመሳተፍ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ነው