የጌዴኦ ባህላዊ መልከአ ምድር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የዕዉቅና መርሃግብር እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጌዴኦ ባህላዊ መልከአ ምድር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የዕዉቅና መርሃግብር በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ በጨልባ ቱቲቲ የባህል ቅርስ እየተካሄደ ይገኛል።
የጌዴኦ ባህላዊ መልከአ ምድር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስነት መመዝገቡ ይታወሳል።
በዓለም ቅርስነት የተመዘገበዉ የጌዴኦ ባህላዊ መልከዓ ምድር ቅርስ በዉስጡ ከስድስት ሺህ በላይ የሚሆኑ ትክል ድንጋይ እና ጥምር ደን እርሻ ይገኙበታል።
በህብረተሰቡ ፍላጎት የተሰራና ባህሉን እሴቱን በማኖሮ እያለማ ጠብቆ ያቆየው ባህላዊ መልከዓ ምድር ቅርስ ነው።
በዕዉቅና አሰጣጥ መርሃ ግብሩ ላይ የፌደራል፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ፍሬህይወት ዱባለ፣ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘውዱ

More Stories
በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ተገቢውን ትኩረት መስጠትና ተግቶ በመስራት ከድህነት መውጣት ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ኢትዮጵያን ለዘመናት ከቆየችበት ቁስል ለማላቀቅ ባለፉት የለውጥ አመታት በርካታ ፖለቲካዊ ተግባራት ማከናወኑን መቻሉ ተገለጸ
ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎችን በመስራታቸው ዘርፈ ብዙ ጠቄሜታ ማግኘታቸውን የአርባምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኮሌጅ ተማሪዎችና መምህራን ገለፁ