የጌዴኦ ባህላዊ መልከአ ምድር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የዕዉቅና መርሃግብር እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጌዴኦ ባህላዊ መልከአ ምድር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የዕዉቅና መርሃግብር በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ በጨልባ ቱቲቲ የባህል ቅርስ እየተካሄደ ይገኛል።
የጌዴኦ ባህላዊ መልከአ ምድር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስነት መመዝገቡ ይታወሳል።
በዓለም ቅርስነት የተመዘገበዉ የጌዴኦ ባህላዊ መልከዓ ምድር ቅርስ በዉስጡ ከስድስት ሺህ በላይ የሚሆኑ ትክል ድንጋይ እና ጥምር ደን እርሻ ይገኙበታል።
በህብረተሰቡ ፍላጎት የተሰራና ባህሉን እሴቱን በማኖሮ እያለማ ጠብቆ ያቆየው ባህላዊ መልከዓ ምድር ቅርስ ነው።
በዕዉቅና አሰጣጥ መርሃ ግብሩ ላይ የፌደራል፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ፍሬህይወት ዱባለ፣ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘውዱ

More Stories
ስፖርተኞች መልካም ስብእና ተላብሰው ውድድራቸውን እያካሄዱ እንደሚገኙ የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ አስታወቀ
የፀረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን ለመከላከል በሚደረገው አገራዊ ጥረት ውስጥ የሚዲያ ባለሙያዎች ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
መምህራን የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅምና መብት በማስጠበቅ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር አስታወቀ