የግብር ከፋዮች የውይይት መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ: ጥር 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብር ከፋዮች የውይይት መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል::
ልማትን ማምጣት ግብርን ከመክፈል ጋር በእጅጉ የተቆራኜ መሆኑን በመድረኩ የተገኙት የከምባታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ መለሰ አጭሶ ተናግረዋል::
በታክስ ሥርዓቱ መሠረት ግብር መክፈል ካልቻልን ጉዳቱ መልሶ የእኛው ነው ያሉ ሲሆን የማስተማር እና የመምከር ሥራ ብዙ ጊዜ መከናወኑንም ገልፀዋል::
ከዚህ በኋላ ሁሉም ግብር ከፋይ ግብርን በአግባቡ በመክፈል የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል::
በግብር ሥርዓቱ ላይ እንቅፋት በሚሆኑ አካሄዶች ላይ ህጉን ተከትሎ እርምጃ ይወሰዳልም ብለዋል::
የዱራሜ ከተማ በክልሉ ካሉ የማእከል ከተሞች አንዷ በመሆኗ ይህን የሚመጥን እድገት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል::
የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ደግሞ ግብር መክፈል ወሳኝነት ያለው ነው ብለዋል ዋና አስተዳዳሪው::
ያለ ደረሰኝ ግብይት መፈፀም፣ የንግድ ፈቃድ አለማውጣት እና ደረሰኝ የመጠየቅ ልምድ አለመዳበር በገቢ ዘርፍ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች መሆናቸው ተገልጿል::
በውይይት መድረኩ ግብር ከፋዮች፣ የከተማ አስተዳደር፣ የዞንና የክልል የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በህገወጥ ንግድ ላይ በተሰማሩና ያላግባብ የዋጋ ጭማሪ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ
በጀት ዓመቱ ከ3 ነጥብ 8 ቢልዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለጸ
የመንግስት በጀት ለታለመለት ዓላማ በአግባቡ ሊውል እንደሚገባ ተገለጸ