የግብር ከፋዮች የውይይት መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ: ጥር 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብር ከፋዮች የውይይት መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል::
ልማትን ማምጣት ግብርን ከመክፈል ጋር በእጅጉ የተቆራኜ መሆኑን በመድረኩ የተገኙት የከምባታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ መለሰ አጭሶ ተናግረዋል::
በታክስ ሥርዓቱ መሠረት ግብር መክፈል ካልቻልን ጉዳቱ መልሶ የእኛው ነው ያሉ ሲሆን የማስተማር እና የመምከር ሥራ ብዙ ጊዜ መከናወኑንም ገልፀዋል::
ከዚህ በኋላ ሁሉም ግብር ከፋይ ግብርን በአግባቡ በመክፈል የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል::
በግብር ሥርዓቱ ላይ እንቅፋት በሚሆኑ አካሄዶች ላይ ህጉን ተከትሎ እርምጃ ይወሰዳልም ብለዋል::
የዱራሜ ከተማ በክልሉ ካሉ የማእከል ከተሞች አንዷ በመሆኗ ይህን የሚመጥን እድገት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል::
የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ደግሞ ግብር መክፈል ወሳኝነት ያለው ነው ብለዋል ዋና አስተዳዳሪው::
ያለ ደረሰኝ ግብይት መፈፀም፣ የንግድ ፈቃድ አለማውጣት እና ደረሰኝ የመጠየቅ ልምድ አለመዳበር በገቢ ዘርፍ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች መሆናቸው ተገልጿል::
በውይይት መድረኩ ግብር ከፋዮች፣ የከተማ አስተዳደር፣ የዞንና የክልል የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ እና ያለብክነት ሊሰበሰብ እንደሚገባ የባኮ ዳውላ ኣሪ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አሳሰበ
አርሶ አደሮች በሚሠሩት የእንሰት ችግኝ ብዜት ሥራ በማሳቸው ተክለው የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ሸጠው የገቢ ምንጫቸውን እንዲያሳድጉ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚያስፈልግ ተገለፀ
የቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበራት የህብረተሰቡን የቁጠባ ባህል ከማዳበር ባለፈ ህብረተሰቡ በቆጠበው ልክ ብድር አግኝቶ መልማት እንዲችል ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ