የግብር ከፋዮች የውይይት መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል

የግብር ከፋዮች የውይይት መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል

ሀዋሳ: ጥር 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብር ከፋዮች የውይይት መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል::

ልማትን ማምጣት ግብርን ከመክፈል ጋር በእጅጉ የተቆራኜ መሆኑን በመድረኩ የተገኙት የከምባታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ መለሰ አጭሶ ተናግረዋል::

በታክስ ሥርዓቱ መሠረት ግብር መክፈል ካልቻልን ጉዳቱ መልሶ የእኛው ነው ያሉ ሲሆን የማስተማር እና የመምከር ሥራ ብዙ ጊዜ መከናወኑንም ገልፀዋል::

ከዚህ በኋላ ሁሉም ግብር ከፋይ ግብርን በአግባቡ በመክፈል የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል::

በግብር ሥርዓቱ ላይ እንቅፋት በሚሆኑ አካሄዶች ላይ ህጉን ተከትሎ እርምጃ ይወሰዳልም ብለዋል::

የዱራሜ ከተማ በክልሉ ካሉ የማእከል ከተሞች አንዷ በመሆኗ ይህን የሚመጥን እድገት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል::

የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ደግሞ ግብር መክፈል ወሳኝነት ያለው ነው ብለዋል ዋና አስተዳዳሪው::

ያለ ደረሰኝ ግብይት መፈፀም፣ የንግድ ፈቃድ አለማውጣት እና ደረሰኝ የመጠየቅ ልምድ አለመዳበር በገቢ ዘርፍ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች መሆናቸው ተገልጿል::

በውይይት መድረኩ ግብር ከፋዮች፣ የከተማ አስተዳደር፣ የዞንና የክልል የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል::

ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ