የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን እየገመገመ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በጋሞ ዞን በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን እየገመገመ ይገኛል።
በግምገማውም ባለፉት ሰድስት ወራት የተከናወኑ ስራዎች የቀረቡ ሲሆን በዋናነትም የሌማት ትሩፋት፣ የተፋሰስ ስራ፣ የመስኖ ስራዎች እና ሌሎች ፕሮጀክቶች ይገኙበታል።
በሪፖርቱም በዘርፉ ከዞን አቅም በላይ የሆኑ ስራዎች በክልሉ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራም ተጠይቋል።
በግምገማው የክልሉ ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጠንክር ጤንካን ጨምሮ ሌሎች የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የጋሞ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሪት አለሚቱ ዮሴፍ እንዲሁም የዞን የዘርፍ ኃላፊዎቸ ተሳታፊ እየሆኑ ነው።
ቋሚ ኮሚቴው በግምገማውም በዞኑ በሪፖርት የቀረቡ ስራዎችን የመስክ ምልከታ ያደርጋል።
ዘጋቢ፡ ቃለአብ ፀጋዬ

More Stories
የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ እና ያለብክነት ሊሰበሰብ እንደሚገባ የባኮ ዳውላ ኣሪ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አሳሰበ
የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንዳጠናቀቅን ሁሉ የባህር በርን ለማስመለስ የሚደረገውን ጥረት በይበልጥ ማገዝ እና መደገፍ እንደሚገባ ተጠቆመ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ከፌደራል ገንዘብ ሚኒስቴር እና ከክልሉ አመራር አካዳሚ ጋር በመተባበር በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ዙሪያ ለኦዲት ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል