የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን እየገመገመ ነው

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን እየገመገመ ነው

ሀዋሳ፡ ጥር 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በጋሞ ዞን በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን እየገመገመ ይገኛል።

በግምገማውም ባለፉት ሰድስት ወራት የተከናወኑ ስራዎች የቀረቡ ሲሆን በዋናነትም የሌማት ትሩፋት፣ የተፋሰስ ስራ፣ የመስኖ ስራዎች እና ሌሎች ፕሮጀክቶች ይገኙበታል።

በሪፖርቱም በዘርፉ ከዞን አቅም በላይ የሆኑ ስራዎች በክልሉ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራም ተጠይቋል።

በግምገማው የክልሉ ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጠንክር ጤንካን ጨምሮ ሌሎች የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የጋሞ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሪት አለሚቱ ዮሴፍ እንዲሁም የዞን የዘርፍ ኃላፊዎቸ ተሳታፊ እየሆኑ ነው።

ቋሚ ኮሚቴው በግምገማውም በዞኑ በሪፖርት የቀረቡ ስራዎችን የመስክ ምልከታ ያደርጋል።

ዘጋቢ፡ ቃለአብ ፀጋዬ