የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን እየገመገመ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በጋሞ ዞን በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን እየገመገመ ይገኛል።
በግምገማውም ባለፉት ሰድስት ወራት የተከናወኑ ስራዎች የቀረቡ ሲሆን በዋናነትም የሌማት ትሩፋት፣ የተፋሰስ ስራ፣ የመስኖ ስራዎች እና ሌሎች ፕሮጀክቶች ይገኙበታል።
በሪፖርቱም በዘርፉ ከዞን አቅም በላይ የሆኑ ስራዎች በክልሉ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራም ተጠይቋል።
በግምገማው የክልሉ ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጠንክር ጤንካን ጨምሮ ሌሎች የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የጋሞ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሪት አለሚቱ ዮሴፍ እንዲሁም የዞን የዘርፍ ኃላፊዎቸ ተሳታፊ እየሆኑ ነው።
ቋሚ ኮሚቴው በግምገማውም በዞኑ በሪፖርት የቀረቡ ስራዎችን የመስክ ምልከታ ያደርጋል።
ዘጋቢ፡ ቃለአብ ፀጋዬ

More Stories
ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኮረሪማ ምርት እየለማ መሆኑ ተገለጸ
በጎፋ ዞን ከ12 ሺህ በላይ ተማሪዎች ክልላዊ የ6ኛ ክፍል ፈተና እየተሰጠ ነው
የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በመመለስ በኩል ከመንግስት ጥረት ባለፈ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና የጎላ መሆኑን የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ ተናገሩ