በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኣሪ ዞን ግብርና መምሪያ የበልግ፣ የተፋሰስ ልማት እና ቡና ልማት ሥራዎች የፈፃሚ ማዘጋጃ መድረክ ተካሄደ
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ እንደገለፁት ግብርና ለሀገራችን ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እንደመሆኑ ዘርፉን በማዘመን የኑሮ ወድነትን ለማቃለል ከፍ ያለ ምርት በማምረት ብልፅግናችንን ማረጋገጥ ይጠበቅብናል ብለዋል።
አክለውም ባለፉት ጊዜያት የተሰሩ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ ቢሆኑም ከሚጠበቀው አኳያ ቀሪ ሥራዎች መኖራቸውን ገልፀው፤ የአከባቢዎችን እምቅ አቅም በመለየት እንደሀገር የተያዙ የሌማት ትሩፋት ክላስተሮችን ማስፋትና ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
በተጨማሪም የተፋሰስና የበልግ ሥራዎችን በማጠናከር የሚጠበቀውን ውጤት ለማምጣት ሁሉም አካላት እንዲረባረቡም አሳስበዋል።
የኣሪ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታፈሰ ተስፋዬ በበኩላቸው ዞናችን ለግብርናው ልማት ምቹ በመሆኑ ዘርፉን ወጤታማ ለማድረግ ፈፃሚውን በንቅናቄ መምራት አስፈላጊ መሆኑን አሰገንዝበዋል።
በመድረኩም ለተግባሩ ማስጀመሪያ የተለያዩ መነሻ ሰነዶች ቀርቦ ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የሀለባ ዞን ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ3 ቢልዮን 293 ሚልዮን ብር ባለይ በጀት አጸደቀ
መስራት እየቻሉ የገንዘብ እጥረት የገጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን ችግሮች ለመፍታት የህብረት ስራ ማህበራት ሚና ቀላል አለመሆኑ ተገለጸ
በስልጤ ልማት ማህበር ለ3ኛ ጊዜ በተዘጋጀው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ከሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር የተሰበሰቡ የአካባቢው ተወላጆች በዞኑ በሚገኙ የላንፉሮ ወረዳና ጦራ ከተማ አስተዳደር ችግኞችን ተክለዋል ።