በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኣሪ ዞን ግብርና መምሪያ የበልግ፣ የተፋሰስ ልማት እና ቡና ልማት ሥራዎች የፈፃሚ ማዘጋጃ መድረክ ተካሄደ
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ እንደገለፁት ግብርና ለሀገራችን ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እንደመሆኑ ዘርፉን በማዘመን የኑሮ ወድነትን ለማቃለል ከፍ ያለ ምርት በማምረት ብልፅግናችንን ማረጋገጥ ይጠበቅብናል ብለዋል።
አክለውም ባለፉት ጊዜያት የተሰሩ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ ቢሆኑም ከሚጠበቀው አኳያ ቀሪ ሥራዎች መኖራቸውን ገልፀው፤ የአከባቢዎችን እምቅ አቅም በመለየት እንደሀገር የተያዙ የሌማት ትሩፋት ክላስተሮችን ማስፋትና ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
በተጨማሪም የተፋሰስና የበልግ ሥራዎችን በማጠናከር የሚጠበቀውን ውጤት ለማምጣት ሁሉም አካላት እንዲረባረቡም አሳስበዋል።
የኣሪ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታፈሰ ተስፋዬ በበኩላቸው ዞናችን ለግብርናው ልማት ምቹ በመሆኑ ዘርፉን ወጤታማ ለማድረግ ፈፃሚውን በንቅናቄ መምራት አስፈላጊ መሆኑን አሰገንዝበዋል።
በመድረኩም ለተግባሩ ማስጀመሪያ የተለያዩ መነሻ ሰነዶች ቀርቦ ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ወጣቶች በዞኑ የሚገኙ ጸጋዎችን ተጠቅመው የገቢ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ገለጸ
በያዝነው ዓመት አስከ ጥቅምት ወር ድረስ 2 መቶ 50 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መላኩን የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የምርምር ተቋማት ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የግብርናውን ስራ ውጤታማ እንዲያደርጉ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ስራ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ኢንስቲትዩት አስታወቀ