በአዉሮፓ ሻምፒዮንስሊግ አራተኛ ዙር የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ አርሰናል፥ ሪያል ማድሪድ እና ባየርንሙኒክ ድል ሲቀናቸዉ ማንቸስተር ዩናይትድ ሽንፈት አስተናግዷል

በሜዳው ሲቪያን ያስተናገደው አርሰናል በሊያንድሮ ትሮሳርድ እና ቡካዮ ሳካ ጎሎች ሁለት ለምንም አሸንፎ ወጥቷል።

ወደ ዴንማርክ አቅንቶ ኮፐንሀገንን የገጠመው ማንቸስተር ዩናይትድ የ4ለ3 ሽንፈት አስተናግዷል።

የማንቸስተር ዩናይትድን 3 ግቦች ራስመስ ሆይሉንድ ሁለቱን ሲያስቆጥር ቀሪዋን ጎል ብሩኖ ፋርናንዴዝ በፍፁም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።

ማርከስ ራሽፎርድ በ42ኛዉ ደቂቃ በቀጥታ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል።

ባየርን ሙኒክ ጋላታሳራይን 2ለ1 አሸንፎ ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱን ሲያረጋግጥ ሁለቱንም የማሸነፊያ ግቦች ሃሪ ኬን አስቆጥሯል።

እስፖርቲንግ ብራጋን በሜዳዉ ያስተናገደው ሪያል ማድሪድ 3ለ0 አሸንፎ ወደ ቀጣይ ዙር ማለፉን አረጋግጧል።

ብራሂም ዲያዝ፥ ቪኒሺዬስ ጁኒዬር እና ሮድሪጎ ጎኤስ ለእስፔኑ ክለብ የማሸነፊያ ግቦችን አስቆጥረዋል።

ማንቸስተር ሲቲ፥ አርቢ ሌይፕዚች፣ ባየርንሙኒክ፣ ሪያል ማድሪድ፥ ሪያል ሶሴዳድ እና ኢንተርሚላን ሁለት ጨዋታ እየቀራቸዉ ጥሎ ማለፉን መቀላቀላቸውን ያረጋገጡ ክለቦች ሆነዋል።

ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ