የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ጽዱና ውብ መሆን እንደሚጠበቅባቸው ተጠቆመ
የኮሬ ዞን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሠራተኞች በወር አንድ ቀን የጽዳት ዘመቻ እንደሚያደርጉም ተገልጿል።
በኮሬ ዞን የኬሌ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ሮቤል ዓለም እንደገለጹት የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ከህክምና ባሻገር ጽዱና ውብ መሆን ለሠራተኞችም ሆነ ለተገልጋዮች የስነልቦና እና የአእምሮ እርካታን ያስገኛል።
በሆስፒታሉ የጥራት ማሻሻያ ክፍል ተጠሪ አቶ ጥላሁን ሹቴ በበኩላቸው ስለ አካባቢ ንፅህና በቃል ከማስተማር በተግባር ለማሳየት የሆስፒታሉ ሠራተኞች በወር አንድ ቀን የጽዳት ዘመቻ እንደሚያደርጉ ነው የተናገሩት።
አክለውም አቶ ጥላሁን የግልና የአከባቢውን ንጽህና መጠበቅ ከተላላፊ በሽታዎች ራስን ለመከላከል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው አስረድተዋል።
ሲስቴር አንድፍሬ ዮናስና ሉቃስ ታደሰ የሆስፒታሉ የህክምና ባለሙያዎች ሲሆኑ የግልና የአከባቢ ንጽሕናን በመጠበቅ የጤና ባለሙያዎችና ተቋማት መልካም ምሳሌዎች መሆን አለብን ብለዋል።
ካነጋገርናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መምህርት ጥሩወርቅ በቀለ በሆስፒታሉ የተጀመረው የአከባቢ ንፅህና ዘመቻ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በመጠቆም ተገልጋዮችም ከሚያዩት መማር እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ምርጫ መላኩ – ከፍስሃገነት ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎትን ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ለሆኑ እናቶችና ሴቶች ተደራሽ በማድረግ ጤናቸው እንዲጠበቅ በትኩረት መሠራቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለፀ
የነበሩ ችግሮች እየተቀረፉ በመምጣታቸው የተሻለ የጤና አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን በከምባታ ዞን አንዳንድ የዶዮገና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተገልጋዮች ተናገሩ
የህብረተሰቡን የግልና አካባቢ ንጽህና አጠባበቅ ባህል ማሻሻል ላይ ትኩረት ያደረገ ሥራ እየተሠራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ገለጹ