ህፃናትን በወቅቱ በማስከተብ ለተለያዩ በሽታዎች እንዳይጋለጡ እየተሰራ መሆኑን በቡርጂ ዞን ሶያማ ከተማ አስተዳደር ጤና ዩኒት ገለጸ
ከሚወለዱ ህፃናት አንድም ሳይከተብ እንዳይቀር በየቀበሌው ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታቋል።
በሶያማ ከተማ ጤና ጣቢያ ህፃናትን ሲያስከትቡ አግኝተን ካነጋገሪናቸው እናቶች መካከል ወ/ሮ ትዕግስት አወቀ፣ ወ/ሮ ኮሹ ደጀኔ እና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት ከጤና ባለሙያዎች ባገኙት ግንዛቤ መሠረት ክትባቱን ሳያቋርጡ በወቅቱ አገልግሎቱ እየተሰጣቸው በመሆኑ ህፃናቱ ለተለያዩ በሽታዎች እንዳይጋለጡ እንደረዳቸው ተናግረዋል።
ክትባት ሲሰጡ ካገኘናቸው ባለሙያዎች መካከል የሶየማ ከተማ 01 ቀበሌ ጤና ኤክስቴሽን ባለሙያ ወ/ሮ ወርቅነሽ ማሞ ለህፃናት የሚሰጠው ክትባት የተለያዩ በሽታዎች እንደሚከላከል ጠቅሰው፥ ህፃናት በሽታ የመከላከል አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ከመጀመሪያ ጀምረው ሳያቋርጡ መጨረስ እንደሚጠበቅባቸውም አስረድተዋል።
የሶያማ ከተማ አስተዳደር ጤና ዩኒት አስተባባሪ አቶ አየለ ሀይሶ በበኩላቸው በያዝነው በጀት ዓመት ባለፉት 6 ወራት 622 ህፃናት ለማስከተብ አቅደው በዘመቻ መልክ በመሥራት ወደ 743 ህፃናትን በማስከተብ ከዕቅድ በላይ ማሳካታቸውን አንስተዋል።
ዕቅዳቸው ግቡን የመታ ቢሆንም ከህፃናት ቁጥር አንፃር ብዙ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው፣ ራቅ ያሉ ቀበሌያትም በከተማው ሥር በመታቀፋቸው የመንገድ ሁኔታ ምቹ ያለመሆንና የተሽከርካሪ እጥረት ተግዳሮቶች መሆናቸውን የጠቀሱት አስተባባሪው፥ ከህብረተሰቡ እና ከሌሎች ባለድረሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሮቹን ለመፍታት እየሠሩ መሆናቸውን አብራርተዋል።
ዘጋቢ፡ ቦጋለ ሉሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ህፃናትን በወቅቱ በማስከተብ ለተለያዩ በሽታዎች እንዳይጋለጡ እየተሰራ መሆኑን በቡርጂ ዞን ሶያማ ከተማ አስተዳደር ጤና ዩኒት ገለጸ

More Stories
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ በመሰማራታቸው የቤት ፍጆታን ከማሟላት ባሻገር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት አረጋገጡ
ክቡር የሆነውን የሰውን ሕይወት ለመታደግ ደም በመለገስ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የይርጋጨፌ ከተማ ጤና ጽህፈት ቤት አሳሰበ
ለሴቶች ሞት ምክንያት የሆነውን የማህፀን በር ካንሰር ቅድመ ምርመራ በማድረግ መከላከል እንደሚገባ የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ሐኪም ዶ/ር አረጋኸኝ ሙሉጌታ አሳሰቡ