መስዕዋት ለሆኑ ጀግኖቻችን አድናቆት እየቸርን ለመጪው ትውልድ የምትሆን ታላቅ ሀገር እናስረክባለን- አቶ አብርሃም መጫ
ሀዋሳ: ጳጉሜ 02/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) መስዕዋት ለሆኑ ጀግኖቻችን አድናቆት እየቸርን ለመጪው ትውልድ የምትሆን ታላቅ ሀገር እናስረክባለን ሲሉ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሀም መጫ ተናገሩ፡፡
የመስዋዕትነት ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች በሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ይገኛል፡፡
በጀግናው ኮሎኔል በዛብህ አደባባይ በተከበረው የመስዋዕትነት ቀን ላይ የተገኙት የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሀም መጫ ኢትዮጵያ በየዘመናቱ ያጋጠማትን ፈተናዎች በጀግኖች ልጆቿ መስዕዋትነት ከሙሉ ክብሯ ጋር ለዛሬ ቀን አብቅተዋታልና ምስጋና ይገብቸዋል ብለዋል፡፡
ቀኑ የጀግኖቻችንን መስዋዕትነት አስበን የምንውልበት እና በኛ ትውልድም ሀገራችን ከኛ የምትፈልገውን መስዋዕትነት ለመክፈል እና ታሪክ ለማኖር የምንዘጋጅበት ነው ሲሉም አክለዋል፡፡
ላለፉት ድንቅ ጀግኖች አድናቆትን እየቸርን ለመጪው ትውልድ የምትሆን ታላቅ ሀገርም እናስረክባለን ነው ያሉት አቶ አብርሀም፡፡
መስዋዕትነት ዳር ድንበርን ከማስጠበቅ ባለፈ ከውስጥና ከውጭ ሀገርን የሚፈትን አደጋ በጋራ በመከላከል ጀግንነትን በተግባር ማሳየት እና ሀገርን በልማት ጎዳና ወደ ከፍታ መውሰድ በመሆኑ ይህን መፈፀም ከኛ ይጠበቃል ብለዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር