የርገን ክሎፕ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ለመሆን ተስማሙ

የርገን ክሎፕ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ለመሆን ተስማሙ

ሀዋሳ: ሰኔ 28/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የቀድሞ የሊቨርፑል አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ለመሾም ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።

የርገን ክሎፕ በገዛ ፈቃዳቸው ከብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝነት የተሰናበቱትን አሰልጣኝ ጁሊያን ናግልስማንን ተክተው የሀገራቸውን ብሔራዊ ቡድን ለማሰልጠን መስማማታቸውን ፋብሪዚዮ ሮማኖ ዘግቧል።

ክሎፕ የመርሲሳይዱን ክለብ ሊቨርፑልን ለሰባት ዓመታት በዋና አሰልጣኝነት ከማምራታቸው በተጨማሪ ሌሎች 6 ክለቦችን በሀላፊነት መርተዋል።

ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ