የኑሮ ውድነት ለመቋቋም በአጭር ጊዜ የሚደርሱ የጓሮ አትክልቶችን እያለማን ነው – በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ሞዴል አርሶአደሮች
እያጋጠመው ያለውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋም በአጭር ጊዜ የሚደርሱ ሰብሎች ወጪውን ከመቀንስ ያለፈ የገቢ ምንጭ እየሆነ መጥቷል አሉ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ሞዴል አርሶአደሮች ፡፡
የሞዴል አርሶአደሮችን ተሞክሮ በማስፋፋት ለገበያ የሚበቃ ምርት በማምረት የኑሮ ውድነትን ችግር ለማቃለል በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የወረዳው ግብርና ልማት ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡
አቶ ፋንታሁን ተክለ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ የዳራሮ ቀበሌ ታታሪ አርሶአደር ናቸው፡፡መተዳደሪያቸው ግብርና ሥራ በመሆኑ የተለያዩ ምርት በማምረት ከምግብ ፈጆታ ያለፈው ምርቱን ለገበያ በማቅረብ በሚያገኙት ገቢ በኑሮአቸው መሻሻሎችን ማየታቸውንና ልጆቻቸውን በአግባቡ ለማስተማር ማብቃታቸውን ተናግረዋል፡፡
ከቋሚ ተክል ጀምሮ እስከ ጓሮ አትክልት በማምረት ወጪውን ከመቆጠብ ባለፈ ማር፣ ቡናና ቆጮ ለገበያ በማቅረብ በአመት ከፍተኛ ውጤት እያገኙ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
አርሶአደሩ ከባህላዊ ንብ ማነብ ሥራ ወደ ዘመናዊ ተሸጋግሯል፡፡ በዚህም ጠቀም ያለው ገቢ እያገኙ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡
አቶ ፋንታሁን የግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበረ ጠቅሰው በአከባቢው ሌሎች አርሶአደሮችን እንደ እርሱ ሞዴል ለማድረግ ተሞክሮአቸውን በማካፈል ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል
የይርጋጨፌ ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክፍለ ጅግሦ እንደ ሀገር የተጀመረው ምግቤን ከጓሮዬ ተግባርን በማጠናከር የኑሮ ውድነት ለማረጋጋት ቀጣይነት ባለው መልኩ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል
በተለይም የኑሮ ውድነት ለማረጋጋት ከሚሠሩ ሥራዎች መካከል በአጭር ጊዜ የሚደርሱ ሰብሎች በስፋት እየተሠራ ነው ያሉት አቶ ክፍለ በዚህም ጽ/ቤቱ የግብዓት ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ በኤክስቴንሽን ባለሙያ ተገቢ ድጋፍ በማድረግ ተሞክሮአቸውን ለማስፋፋት እየሠሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ ፡ እምነት ሽፈራው- ከፍስሀ ገነት ጣቢያችን

More Stories
የብራይት ፕሮጀክት የሴቶችንና ህፃናትን የስራ ጫና ከማቃለል ባሻገር የንፁህ መጠጥ ውሀ ተደራሽነት ላይ የሚመታይ ተግባር ማከናወኑን የጋሞ ዞን ውሀና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጥናታቸው በተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች ላይ ያተኮረ የማረጋገጫ ወርክሾፕ እና የርክክብ መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል
የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት የቤት ልማት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ